
ጂንካ፤ ግንቦት 6/2017(ኢዜአ)፦ ከቱሪዝም ኢንዱስትሪው የሚገኘውን ሀገራዊ ጥቅም ለማሳደግ በሳይንሳዊ ምርምር ማጎልበትና በሰው ሰራሽ አስተውሎት በመደገፍ ማዘመን እንደሚገባ የዘርፉ ምሁራን ገለጹ።
በጂንካ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት በቱሪዝም ላይ ያተኮረ የጥናትና ምርምር ኮንፍረንስ ተካሂዷል።
በኮንፍረንሱ የምርምር ስራዎቻቸውን ያቀረቡ የዘርፉ ተመራማሪዎች ከቱሪዝም ኢንዱስትሪው የሚገኘውን ሀገራዊ ጥቅም ለማሳደግ በሳይንሳዊ ምርምር ማጎልበትና በሰው ሰራሽ አስተውሎት መደገፍ ይገባል ብለዋል።
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የባህል ተመራማሪ ፕሮፌሰር ይስሃቅ ከቸሮ ቱሪዝምን በምርምርና በሰው ሰራሽ አስተውሎት ማዘመን በሚል ርዕስ ጥናታዊ ፅሑፍ አቅርበዋል።
ኢትዮጵያ በቱሪዝም ሀብቷ ከፍተኛ አቅም ያላት ብትሆንም ከዘርፉ የሚገባትን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እያገኘች አለመሆኑን ጠቁመዋል።
እንደ ኬኒያ ያሉ ሀገራት ሰው ሰራሽ አስተውሎትን በመጠቀም ከቱሪዝም ተጠቃሚ መሆን ችለዋል ያሉት ተመራማሪው፤ ኢትዮጵያም ከዘርፉ ተገቢውን ጥቅም ለማግኘት የምርምር ውጤቶችን ከሰው ሰራሽ አስተውሎት ጋር በማቀናጀት መጠቀም እንዳለባት አመልክተዋል።

የጂንካ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ፣ የምርምር፣ የቴክኖሎጂ ሽግግር እና የማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዚዳንት ተወካይ አቶ ኢብራሂም ጀማል በበኩላቸው፤ የቱሪዝም ኢንዱስትሪውን ለማነቃቃትና ለማዘመን ሳይንሳዊ ምርምሮች ትልቅ ጠቀሜታ እንዳላቸው ገልጸዋል።
ቱሪዝም የዩኒቨርሲቲው ዋነኛ የትኩረት መስክ እንደሆነ ገልጸው፥ ዘርፉን በሳይንሳዊ ምርምር በማጎልበት ከቱሪዝም ኢንዱስትሪው የሚገኘውን ሀብት ለማሳደግ ዩኒቨርሲቲው እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ወይኒቱ መልኩ በበኩላቸው፥ በክልሉ ያሉ በርካታ የቱሪስት መስህቦችን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ለማሳደግ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025