
ጂንካ፤ ግንቦት 6/2017(ኢዜአ)፦ ከቱሪዝም ኢንዱስትሪው የሚገኘውን ሀገራዊ ጥቅም ለማሳደግ በሳይንሳዊ ምርምር ማጎልበትና በሰው ሰራሽ አስተውሎት በመደገፍ ማዘመን እንደሚገባ የዘርፉ ምሁራን ገለጹ።
በጂንካ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት በቱሪዝም ላይ ያተኮረ የጥናትና ምርምር ኮንፍረንስ ተካሂዷል።
በኮንፍረንሱ የምርምር ስራዎቻቸውን ያቀረቡ የዘርፉ ተመራማሪዎች ከቱሪዝም ኢንዱስትሪው የሚገኘውን ሀገራዊ ጥቅም ለማሳደግ በሳይንሳዊ ምርምር ማጎልበትና በሰው ሰራሽ አስተውሎት መደገፍ ይገባል ብለዋል።
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የባህል ተመራማሪ ፕሮፌሰር ይስሃቅ ከቸሮ ቱሪዝምን በምርምርና በሰው ሰራሽ አስተውሎት ማዘመን በሚል ርዕስ ጥናታዊ ፅሑፍ አቅርበዋል።
ኢትዮጵያ በቱሪዝም ሀብቷ ከፍተኛ አቅም ያላት ብትሆንም ከዘርፉ የሚገባትን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እያገኘች አለመሆኑን ጠቁመዋል።
እንደ ኬኒያ ያሉ ሀገራት ሰው ሰራሽ አስተውሎትን በመጠቀም ከቱሪዝም ተጠቃሚ መሆን ችለዋል ያሉት ተመራማሪው፤ ኢትዮጵያም ከዘርፉ ተገቢውን ጥቅም ለማግኘት የምርምር ውጤቶችን ከሰው ሰራሽ አስተውሎት ጋር በማቀናጀት መጠቀም እንዳለባት አመልክተዋል።

የጂንካ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ፣ የምርምር፣ የቴክኖሎጂ ሽግግር እና የማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዚዳንት ተወካይ አቶ ኢብራሂም ጀማል በበኩላቸው፤ የቱሪዝም ኢንዱስትሪውን ለማነቃቃትና ለማዘመን ሳይንሳዊ ምርምሮች ትልቅ ጠቀሜታ እንዳላቸው ገልጸዋል።
ቱሪዝም የዩኒቨርሲቲው ዋነኛ የትኩረት መስክ እንደሆነ ገልጸው፥ ዘርፉን በሳይንሳዊ ምርምር በማጎልበት ከቱሪዝም ኢንዱስትሪው የሚገኘውን ሀብት ለማሳደግ ዩኒቨርሲቲው እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ወይኒቱ መልኩ በበኩላቸው፥ በክልሉ ያሉ በርካታ የቱሪስት መስህቦችን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ለማሳደግ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...
Aug 28, 2026
መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...
Aug 18, 2026
ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...
Aug 10, 2026
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...
Jul 20, 2026