ቴፒ፤ ግንቦት 6/2017(ኢዜአ)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የህብረተሰቡን የልማት ፍላጎት ለማሟላት ገቢን አሟጦ መሰብሰብ እንደሚገባ የክልሉ ምክር ቤት አስታወቀ።
በሸካ ዞን በህብረተሰቡ ተሳትፎ ገቢና ልማት ማጠናከር በሚቻልበት ጉዳይ ላይ ያተኮረ ህዝባዊ የውይይት መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሂዷል።
በመድረኩ ላይ የተገኙት በክልሉ ምክር ቤት የበጀትና ፋይናንስ አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወይዘሮ የኋላሸት በላይነህ እንደገለጹት በክልሉ ልማትን አጠናክሮ ለማስቀጠል በቅንጅት እየተሠራ ነው።
የልማት ሥራዎች የሕዝብን ፍላጎት መሠረት አድርገው እንዲተገበሩ ምክር ቤቱ ከአስፈጻሚ አካላት ጋር በቅርበት እየሠራ መሆኑን ተናግረዋል።
በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ ገቢን አሟጦ የመሰብሰብ ሥራው ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አስገንዝበዋል።
ልማትን ለማፋጠን የክልሉን ሰላም አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ ገልጸው፣ መድረኩ ልማትና ገቢ የተሳሰሩ መሆናቸውን ለህብረተሰቡ ለማስገንዘብ ጠቀሜታ እንዳለው ተናግረዋል።
ህብረተሰቡ ግብሩን በአግባቡ ከመክፈል ባለፈ የልማት ተሳትፎውን በማጠናከር የበኩሉን እንዲወጣም አስገንዝበዋል።
የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሕይወት አሰግድ በበኩላቸው የክልሉን ወጪ በራስ አቅም ለመሸፈን የሚደረገውን ጥረት ለማሳካት የኅብረተሰቡ ሚና ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።
በተለይም ከተረጂነት መውጣት ገቢ ትልቅ ትርጉም እንዳለው ጠቅሰው፣ ግብርን በታማኝነት በመክፈል ልማትን መደገፍ ከሁሉም ዜጋ ይጠበቃል ብለዋል።
የመንግሥት ገቢ በትክክል ተሰብስቦ ለልማት እንዲውልም ህብረተሰቡ በየደረጃው ሕገወጥ አሠራርን መታገል እንዳለበትም አሳስበዋል።
በቴፒ ከተማ በተካሄደው የውይይት መድረክ የተገኙት የክልሉ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ሰላምና ልማጥን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይም ገለጻ አድርገዋል።
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025
ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...
Feb 8, 2025