
ቴፒ፤ ግንቦት 6/2017(ኢዜአ)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የህብረተሰቡን የልማት ፍላጎት ለማሟላት ገቢን አሟጦ መሰብሰብ እንደሚገባ የክልሉ ምክር ቤት አስታወቀ።
በሸካ ዞን በህብረተሰቡ ተሳትፎ ገቢና ልማት ማጠናከር በሚቻልበት ጉዳይ ላይ ያተኮረ ህዝባዊ የውይይት መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሂዷል።

በመድረኩ ላይ የተገኙት በክልሉ ምክር ቤት የበጀትና ፋይናንስ አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወይዘሮ የኋላሸት በላይነህ እንደገለጹት በክልሉ ልማትን አጠናክሮ ለማስቀጠል በቅንጅት እየተሠራ ነው።
የልማት ሥራዎች የሕዝብን ፍላጎት መሠረት አድርገው እንዲተገበሩ ምክር ቤቱ ከአስፈጻሚ አካላት ጋር በቅርበት እየሠራ መሆኑን ተናግረዋል።
በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ ገቢን አሟጦ የመሰብሰብ ሥራው ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አስገንዝበዋል።
ልማትን ለማፋጠን የክልሉን ሰላም አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ ገልጸው፣ መድረኩ ልማትና ገቢ የተሳሰሩ መሆናቸውን ለህብረተሰቡ ለማስገንዘብ ጠቀሜታ እንዳለው ተናግረዋል።
ህብረተሰቡ ግብሩን በአግባቡ ከመክፈል ባለፈ የልማት ተሳትፎውን በማጠናከር የበኩሉን እንዲወጣም አስገንዝበዋል።

የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሕይወት አሰግድ በበኩላቸው የክልሉን ወጪ በራስ አቅም ለመሸፈን የሚደረገውን ጥረት ለማሳካት የኅብረተሰቡ ሚና ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።
በተለይም ከተረጂነት መውጣት ገቢ ትልቅ ትርጉም እንዳለው ጠቅሰው፣ ግብርን በታማኝነት በመክፈል ልማትን መደገፍ ከሁሉም ዜጋ ይጠበቃል ብለዋል።
የመንግሥት ገቢ በትክክል ተሰብስቦ ለልማት እንዲውልም ህብረተሰቡ በየደረጃው ሕገወጥ አሠራርን መታገል እንዳለበትም አሳስበዋል።
በቴፒ ከተማ በተካሄደው የውይይት መድረክ የተገኙት የክልሉ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ሰላምና ልማጥን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይም ገለጻ አድርገዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026