
ቴፒ፤ ግንቦት 6/2017(ኢዜአ)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የህብረተሰቡን የልማት ፍላጎት ለማሟላት ገቢን አሟጦ መሰብሰብ እንደሚገባ የክልሉ ምክር ቤት አስታወቀ።
በሸካ ዞን በህብረተሰቡ ተሳትፎ ገቢና ልማት ማጠናከር በሚቻልበት ጉዳይ ላይ ያተኮረ ህዝባዊ የውይይት መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሂዷል።

በመድረኩ ላይ የተገኙት በክልሉ ምክር ቤት የበጀትና ፋይናንስ አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወይዘሮ የኋላሸት በላይነህ እንደገለጹት በክልሉ ልማትን አጠናክሮ ለማስቀጠል በቅንጅት እየተሠራ ነው።
የልማት ሥራዎች የሕዝብን ፍላጎት መሠረት አድርገው እንዲተገበሩ ምክር ቤቱ ከአስፈጻሚ አካላት ጋር በቅርበት እየሠራ መሆኑን ተናግረዋል።
በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ ገቢን አሟጦ የመሰብሰብ ሥራው ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አስገንዝበዋል።
ልማትን ለማፋጠን የክልሉን ሰላም አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ ገልጸው፣ መድረኩ ልማትና ገቢ የተሳሰሩ መሆናቸውን ለህብረተሰቡ ለማስገንዘብ ጠቀሜታ እንዳለው ተናግረዋል።
ህብረተሰቡ ግብሩን በአግባቡ ከመክፈል ባለፈ የልማት ተሳትፎውን በማጠናከር የበኩሉን እንዲወጣም አስገንዝበዋል።

የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሕይወት አሰግድ በበኩላቸው የክልሉን ወጪ በራስ አቅም ለመሸፈን የሚደረገውን ጥረት ለማሳካት የኅብረተሰቡ ሚና ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።
በተለይም ከተረጂነት መውጣት ገቢ ትልቅ ትርጉም እንዳለው ጠቅሰው፣ ግብርን በታማኝነት በመክፈል ልማትን መደገፍ ከሁሉም ዜጋ ይጠበቃል ብለዋል።
የመንግሥት ገቢ በትክክል ተሰብስቦ ለልማት እንዲውልም ህብረተሰቡ በየደረጃው ሕገወጥ አሠራርን መታገል እንዳለበትም አሳስበዋል።
በቴፒ ከተማ በተካሄደው የውይይት መድረክ የተገኙት የክልሉ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ሰላምና ልማጥን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይም ገለጻ አድርገዋል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025