አዲስ አበባ፤ግንቦት 8/2017(ኢዜአ)፦ከ10 ሺህ በላይ ተሳታፊዎች የሚታደሙበትና በምስራቅ አፍሪካ ትልቁ አለምአቀፍ የቴክኖሎጂ ኤክስፖ በአዲስ አበባ ይካሄዳል።
ETEX 2025 ኤክስፖ ከአዳዲስ ቴክኖሎጂ አቅርቦት ጋር ተያይዞ በአለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅና ያተረፉ ኩባንያዎች የሚሳተፉበት የቴክኖሎጂ ኤክስፖ ነው።
በኤክስፖው ከፍተኛ ተቀባይነትና ዕውቅና ያላቸው ከመቶ በላይ የአገር ውስጥና የውጭ የቴክኖሎጂ አቅራቢዎች ምርትና አገልግሎታቸውን ያስተዋውቃሉ።
በአዲስ አለምአቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ዛሬ በይፋ በሚከፈተው የቴክኖሎጂ ኤክስፖ ከተለያዩ ሀገራት የሚመጡ 10 ሺህ ተሳታፊዎች ይታደማሉ።
ኤክስፖውን ያዘጋጁት የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደርና የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የሳይበር ደህንነት ተቋም ጋር በመተባበር ነው።
በኤክስፖው የአገር ውስጥና አለምአቀፍ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች ምርትና አገልግሎታቸውን ከማስተዋወቅ ባለፈ የተለያዩ የፓናል ውይይቶች ይካሄዳሉ።
የሳይበር ደህንነት፣አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ፣ስማርቲ ሲቲና ዲጂታል ቴክኖሎጂ ላይ ያተኮሩ ውይይቶችን ጨምሮ የሮቦቲክስና ሌሎች የቴክኖሎጂ ውድድሮች የሚካሄዱበት ነው።
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025
ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...
Feb 8, 2025