
አዲስ አበባ፤ግንቦት 8/2017(ኢዜአ)፦ከ10 ሺህ በላይ ተሳታፊዎች የሚታደሙበትና በምስራቅ አፍሪካ ትልቁ አለምአቀፍ የቴክኖሎጂ ኤክስፖ በአዲስ አበባ ይካሄዳል።
ETEX 2025 ኤክስፖ ከአዳዲስ ቴክኖሎጂ አቅርቦት ጋር ተያይዞ በአለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅና ያተረፉ ኩባንያዎች የሚሳተፉበት የቴክኖሎጂ ኤክስፖ ነው።
በኤክስፖው ከፍተኛ ተቀባይነትና ዕውቅና ያላቸው ከመቶ በላይ የአገር ውስጥና የውጭ የቴክኖሎጂ አቅራቢዎች ምርትና አገልግሎታቸውን ያስተዋውቃሉ።
በአዲስ አለምአቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ዛሬ በይፋ በሚከፈተው የቴክኖሎጂ ኤክስፖ ከተለያዩ ሀገራት የሚመጡ 10 ሺህ ተሳታፊዎች ይታደማሉ።
ኤክስፖውን ያዘጋጁት የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደርና የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የሳይበር ደህንነት ተቋም ጋር በመተባበር ነው።
በኤክስፖው የአገር ውስጥና አለምአቀፍ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች ምርትና አገልግሎታቸውን ከማስተዋወቅ ባለፈ የተለያዩ የፓናል ውይይቶች ይካሄዳሉ።
የሳይበር ደህንነት፣አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ፣ስማርቲ ሲቲና ዲጂታል ቴክኖሎጂ ላይ ያተኮሩ ውይይቶችን ጨምሮ የሮቦቲክስና ሌሎች የቴክኖሎጂ ውድድሮች የሚካሄዱበት ነው።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026