አዲስ አበባ፤ ግንቦት 7/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የልማት ግቦቿን ለማሳካት በምታደርገው ጥረት የአውሮፓ ሕብረት የልማት አጋሮች ድጋፍ እንደሚያደርጉ በኢትዮጵያ የአውሮፓ ሕብረት አምባሳደር ሶፊ ፍሮም-ኢመስበርገር ገለጹ።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራርመዋል።
ስምምነቱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥ ሰለሞን ደስታ እና የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ የኢትዮጵያና የአፍሪካ ሕብረት ተወካይ ሌይላ ትራውሬ ፈርመውታል።
በዚሁ ወቅት በኢትዮጵያ የአውሮፓ ሕብረት አምባሳደር ሶፊ ፍሮም-ኢመስበርገር፣ የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ተነሳሽነቶችን ይደግፋል ብለዋል።
በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና በአውሮፓ ልማት ባንክ የተደረገው ስምምነትም የኢትዮጵያን ልማትና የፋይናንስ ሥርዓት መደገፍ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።
በቀጣይም የአውሮፓ ሕብረት የልማት አጋሮች ኢትዮጵያ የልማት ግቦቿን ለማሳካት ለምታደርገው ጥረት ድጋፉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥ ሰለሞን ደስታ፤ የመግባቢያ ስምምነቱ የሁለቱን ባንኮች ትብብር ለማጠናከር ጉልህ ሚና ይኖረዋል ብለዋል።
ስምምነቱ ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት የምታደርገውን ጥረት መደገፍ የሚስችል መሆኑን ገልጸዋል።
የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ የኢትዮጵያና የአፍሪካ ሕብረት ተወካይ ሌይላ ትራውሬ ስምምነቱ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የስራ መሪነት ተግባራዊ የሚደረግ ነው ብለዋል።
በስምምነቱ መሰረትም ኢትዮጵያ የአረንጓዴ ኢኮኖሚና ፋይናንስ ሥርዓትን ለመገንባት ለምታደርገው ጥረት ድጋፍ የሚደረግ መሆኑንም አንስተዋል።
በኢትዮጵያ የጀርመን አምባሳደር ጄንስ ሀኔፌልድን፤ የጀርመን መንግስት በአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን ለመቋቋም የሚደረጉ ጥረቶችን ይደግፋል ብለዋል።
ኢትዮጵያም አረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት በምታደርገው ጥረት ጀርመን ቀጣይነት ያለው ድጋፍ እንደምታደርግ አረጋግጠዋል።
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025
ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...
Feb 8, 2025