የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ኢትዮጵያ የልማት ግቦቿን ለማሳካት በምታደርገው ጥረት የአውሮፓ ሕብረት የልማት አጋሮች ድጋፍ ያደርጋሉ - አምባሳደር ሶፊ ፍሮም-ኢመስበርገር

May 16, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 7/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የልማት ግቦቿን ለማሳካት በምታደርገው ጥረት የአውሮፓ ሕብረት የልማት አጋሮች ድጋፍ እንደሚያደርጉ በኢትዮጵያ የአውሮፓ ሕብረት አምባሳደር ሶፊ ፍሮም-ኢመስበርገር ገለጹ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራርመዋል።

ስምምነቱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥ ሰለሞን ደስታ እና የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ የኢትዮጵያና የአፍሪካ ሕብረት ተወካይ ሌይላ ትራውሬ ፈርመውታል።

በዚሁ ወቅት በኢትዮጵያ የአውሮፓ ሕብረት አምባሳደር ሶፊ ፍሮም-ኢመስበርገር፣ የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ተነሳሽነቶችን ይደግፋል ብለዋል።

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና በአውሮፓ ልማት ባንክ የተደረገው ስምምነትም የኢትዮጵያን ልማትና የፋይናንስ ሥርዓት መደገፍ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።

በቀጣይም የአውሮፓ ሕብረት የልማት አጋሮች ኢትዮጵያ የልማት ግቦቿን ለማሳካት ለምታደርገው ጥረት ድጋፉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥ ሰለሞን ደስታ፤ የመግባቢያ ስምምነቱ የሁለቱን ባንኮች ትብብር ለማጠናከር ጉልህ ሚና ይኖረዋል ብለዋል።

ስምምነቱ ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት የምታደርገውን ጥረት መደገፍ የሚስችል መሆኑን ገልጸዋል።

የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ የኢትዮጵያና የአፍሪካ ሕብረት ተወካይ ሌይላ ትራውሬ ስምምነቱ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የስራ መሪነት ተግባራዊ የሚደረግ ነው ብለዋል።

በስምምነቱ መሰረትም ኢትዮጵያ የአረንጓዴ ኢኮኖሚና ፋይናንስ ሥርዓትን ለመገንባት ለምታደርገው ጥረት ድጋፍ የሚደረግ መሆኑንም አንስተዋል።

በኢትዮጵያ የጀርመን አምባሳደር ጄንስ ሀኔፌልድን፤ የጀርመን መንግስት በአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን ለመቋቋም የሚደረጉ ጥረቶችን ይደግፋል ብለዋል።

ኢትዮጵያም አረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት በምታደርገው ጥረት ጀርመን ቀጣይነት ያለው ድጋፍ እንደምታደርግ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026