የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ኢትዮጵያ የድሮን ትርኢት አካሄደች

May 19, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 8/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ 1 ሺህ 500 ድሮኖች የተሳተፉበት የድሮን የአየር ላይ ትርኢት አካሄደች።

በትሪኢቱ የተሳተፉ የድሮኖች ቁጥር በአፍሪካ የመጀመሪያ እንደሚያደርገውም ተገልጿል።

በትርኢቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፤ የመንግሥት ከፍተኛ አመራሮች፣ ዲፕሎማቶችና ጥሪ የተደረገላቸው በርካታ እንግዶች ታድመዋል።

የድሮን ትርኢቱ የኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ኤክስፖ 2025 አካል ሲሆን በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትና በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር በጋራ የተዘጋጀ መሆኑም ተገልጿል።

ድሮኖቹም ዲጂታል ኢትዮጵያ፣ አረንጓዴ አሻራ እና የተለያዩ ኢኒሼቲቮችን የሚገልፁ ትርኢቶችን አሳይተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.