የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የዲጂታል አትዮጵያ ግንባታን ለማፋጠን የቴክኖሎጂ ልማት ስራን አጠናክረን እንቀጥላለን-የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ኤክስፖ ተሳታፊዎች

May 19, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 10/2017(ኢዜአ)፡-የዲጂታል አትዮጵያ ግንባታን ለማፋጠን አገር በቀል ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎችን የማልማት ስራን አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉ የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ኤክስፖ ተሳታፊዎች ገለጹ።

ኤክስፖው በርካታ ልምድ ያገኙበት መሆኑንም ገልጸዋል።

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር እና የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በጋራ ያዘጋጁት በምስራቅ አፍሪካ ትልቁ ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ኤክስፖ 2025 በአዲስ አበባ ተከፍቷል፡፡

በብሔራዊ የዲጂታል መታወቂያ ሱፐርቫይዘር የሆኑት በርናባስ መኮንን፤ ኢትዮጵያ በዲጂታል መታወቂያ እያከናወነችው ያለው ውጤታማ ተግባር በኤክስፖው መቅረቡን ተናግረዋል፡፡

ለኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታና ሁለንተናዊ ዕድገት መፋጠን የዲጂታል መታወቂያ ተደራሽነት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚያደርግ አመልክተዋል፡፡

ኢትዮጵያ በዲጂታል መታወቂያ እየሰራች ያለው ስራ ከአፍሪካ ትልቁ መሆኑን አንስተው፤ በመጪው ሳምንት በሚጀመረው አይዲ-4 አፍሪካ ኤክስፖ ላይ በቀጣይ የማስተዋወቅ ስራ ይሰራል ብለዋል።


በኤክስፖው ከተሳተፉት መካከል ከአማራ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የዌብና አፕሊኬሽን ቲም ሊደር ደጀኔ ሀብቴ እንደገለጹት፤ በኤክስፖው በክልሉ አገልግሎት ላይ የዋሉ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ውጤቶች ቀርበዋል፡፡

በተለይ በኮሪደር ልማት የተሰሩ ስራዎች እና መሰረተ ልማቶቹን ተከትሎ የተገጠሙ ዲጂታል ካሜራዎች እንዲሁም የስማርት ሩም ቴክኖሎጂዎችን ማቅረባቸውን አንስተዋል፡፡

በኤክስፖው በአማራ ክልል በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን ማሳየት መቻላቸውን አመልክተው፤ በተለይ በተለያዩ የአገሪቷ ክልሎች የተከናወኑ ውጤታማ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ስራዎች መመልከታቸውንም ገልጸዋል።

በክልሉ የዲጂታል ቴክኖሎጂን ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ ልምድ መቅሰማቸውን ጠቅሰው፤ ዲጂታል ኢትዮጵያን ለማፋጠን እንተጋለን ብለዋል፡፡

በሶፍትዌር ማልማት ላይ የተሰማራ ሀገር በቀል የግል ድርጅትን በኤክስፖው ይዘው የቀረቡት መኮንን ትኩ በበኩላቸው፥ ኤክስፖው ኢትዮጵያ በዲጂታል ልማት የደረሰችበትን ከፍታ ያሳየ ነው ብለዋል።


መንግስት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት ተከትሎ በዲጂታል ቴክኖሎጂ ከፍተኛ ለውጥ እየተመዘገበ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በዘርፉ ለተሰማሩ የግሉ ዘርፍ ተዋናዮችም ትልቅ ድጋፍና ትኩረት መሰጠቱን ጨምረው አንስተዋል።

ተሳታፊዎቹ የዲጂታል ኢትዮጵያ ግንባታን ለማፋጠን በዘርፉ እያከናወኑ ያሉትን ተግባር አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026