
ወላይታ ሶዶ፤ግንቦት 8/2017 (ኢዜአ)፦የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የምርምር ውጤቶችን ለባለድርሻ አካላት ተደራሽ በማድረግ ወደ ተግባር ተለውጠው የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት እንዲያጎለብቱ እየሰራ እንደሚገኝ አስታወቀ።
ዩኒቨርሲቲው በኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ዘርፎች የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ማድረግ በሚችሉ ጥናታዊ ምርምሮች ላይ አተኩሮ እንደሚሰራም ተገልጿል።
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ''ተግባር ተኮር ምርምር እና ፈጠራ ስራዎች ለዘላቂ ልማት'' በሚል መሪ ሃሳብ 13ኛ ዓመታዊ ሀገር አቀፍ የምርምር ኮንፈረንስ አካሄዷል።
የዩኒቨርሲቲው ምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚዳንት ዘውድነህ ቶማስ (ዶ/ር) በወቅቱ ለኢዜአ እንዳሉት፥ ዩኒቨርሲቲው የምርምር ውጤቶችን ለባለድርሻ አካላት ተደራሽ በማድረግ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት እንዲያጎለብቱ እየሰራ ነው።
በተጨማሪም የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለሚያጠናክሩ የምርምር ስራዎች ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑንም ምክትል ፕሬዚዳንቱ ጠቁመዋል።
የምርምር ስራዎቹም በአካባቢው የሚካሄዱ የእርሻና የእንስሳት ልማት ስራዎችን በማዘመን በሽታንና የአየር ንብረት ለውጥን በመቋቋም አርሶ አደሩን የተሻለ ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስችሉ ናቸው ብለዋል።
በዩኒቨርሲቲው የተካሄደው የምርምር ኮንፈረንስም የተጠቀሱትን ጨምሮ ሌሎች የምርምር ውጤቶችን ለፖሊሲ አውጪዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በሚጠቅም መልኩ ለማዘጋጀትም እገዛው የጎላ እንደሆነም አንስተዋል።
የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጴጥሮስ ወልደማርያም በበኩላቸው፥ ዩኒቨርሲቲው በአካባቢው በሚሰራቸው ችግር ፈቺ የምርምር ስራዎች የላቀ አገልግሎት ሲሰጥ መቆየቱን ተናግረዋል።
በተለይም በኢኮኖሚው ዘርፍ ግብርናን ማዘመን የሚያስችሉ ምርምሮችና በማህበራዊ መስክም በትምህርትና ጤና ረገድ የማህበረሰቡን ህይወት የሚለውጡ ስራዎች መስራቱን አብራርተዋል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025