የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ዩኒቨርሲቲው የምርምር ውጤቶች ወደ ተግባር ተለውጠው የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት እንዲያጎለብቱ እየሰራ ነው

May 19, 2025

IDOPRESS

ወላይታ ሶዶ፤ግንቦት 8/2017 (ኢዜአ)፦የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የምርምር ውጤቶችን ለባለድርሻ አካላት ተደራሽ በማድረግ ወደ ተግባር ተለውጠው የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት እንዲያጎለብቱ እየሰራ እንደሚገኝ አስታወቀ።


ዩኒቨርሲቲው በኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ዘርፎች የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ማድረግ በሚችሉ ጥናታዊ ምርምሮች ላይ አተኩሮ እንደሚሰራም ተገልጿል።


የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ''ተግባር ተኮር ምርምር እና ፈጠራ ስራዎች ለዘላቂ ልማት'' በሚል መሪ ሃሳብ 13ኛ ዓመታዊ ሀገር አቀፍ የምርምር ኮንፈረንስ አካሄዷል።


የዩኒቨርሲቲው ምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚዳንት ዘውድነህ ቶማስ (ዶ/ር) በወቅቱ ለኢዜአ እንዳሉት፥ ዩኒቨርሲቲው የምርምር ውጤቶችን ለባለድርሻ አካላት ተደራሽ በማድረግ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት እንዲያጎለብቱ እየሰራ ነው።


በተጨማሪም የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለሚያጠናክሩ የምርምር ስራዎች ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑንም ምክትል ፕሬዚዳንቱ ጠቁመዋል።


የምርምር ስራዎቹም በአካባቢው የሚካሄዱ የእርሻና የእንስሳት ልማት ስራዎችን በማዘመን በሽታንና የአየር ንብረት ለውጥን በመቋቋም አርሶ አደሩን የተሻለ ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስችሉ ናቸው ብለዋል።


በዩኒቨርሲቲው የተካሄደው የምርምር ኮንፈረንስም የተጠቀሱትን ጨምሮ ሌሎች የምርምር ውጤቶችን ለፖሊሲ አውጪዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በሚጠቅም መልኩ ለማዘጋጀትም እገዛው የጎላ እንደሆነም አንስተዋል።


የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጴጥሮስ ወልደማርያም በበኩላቸው፥ ዩኒቨርሲቲው በአካባቢው በሚሰራቸው ችግር ፈቺ የምርምር ስራዎች የላቀ አገልግሎት ሲሰጥ መቆየቱን ተናግረዋል።


በተለይም በኢኮኖሚው ዘርፍ ግብርናን ማዘመን የሚያስችሉ ምርምሮችና በማህበራዊ መስክም በትምህርትና ጤና ረገድ የማህበረሰቡን ህይወት የሚለውጡ ስራዎች መስራቱን አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.