
ወላይታ ሶዶ፤ግንቦት 8/2017 (ኢዜአ)፦የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የምርምር ውጤቶችን ለባለድርሻ አካላት ተደራሽ በማድረግ ወደ ተግባር ተለውጠው የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት እንዲያጎለብቱ እየሰራ እንደሚገኝ አስታወቀ።
ዩኒቨርሲቲው በኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ዘርፎች የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ማድረግ በሚችሉ ጥናታዊ ምርምሮች ላይ አተኩሮ እንደሚሰራም ተገልጿል።
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ''ተግባር ተኮር ምርምር እና ፈጠራ ስራዎች ለዘላቂ ልማት'' በሚል መሪ ሃሳብ 13ኛ ዓመታዊ ሀገር አቀፍ የምርምር ኮንፈረንስ አካሄዷል።
የዩኒቨርሲቲው ምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚዳንት ዘውድነህ ቶማስ (ዶ/ር) በወቅቱ ለኢዜአ እንዳሉት፥ ዩኒቨርሲቲው የምርምር ውጤቶችን ለባለድርሻ አካላት ተደራሽ በማድረግ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት እንዲያጎለብቱ እየሰራ ነው።
በተጨማሪም የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለሚያጠናክሩ የምርምር ስራዎች ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑንም ምክትል ፕሬዚዳንቱ ጠቁመዋል።
የምርምር ስራዎቹም በአካባቢው የሚካሄዱ የእርሻና የእንስሳት ልማት ስራዎችን በማዘመን በሽታንና የአየር ንብረት ለውጥን በመቋቋም አርሶ አደሩን የተሻለ ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስችሉ ናቸው ብለዋል።
በዩኒቨርሲቲው የተካሄደው የምርምር ኮንፈረንስም የተጠቀሱትን ጨምሮ ሌሎች የምርምር ውጤቶችን ለፖሊሲ አውጪዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በሚጠቅም መልኩ ለማዘጋጀትም እገዛው የጎላ እንደሆነም አንስተዋል።
የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጴጥሮስ ወልደማርያም በበኩላቸው፥ ዩኒቨርሲቲው በአካባቢው በሚሰራቸው ችግር ፈቺ የምርምር ስራዎች የላቀ አገልግሎት ሲሰጥ መቆየቱን ተናግረዋል።
በተለይም በኢኮኖሚው ዘርፍ ግብርናን ማዘመን የሚያስችሉ ምርምሮችና በማህበራዊ መስክም በትምህርትና ጤና ረገድ የማህበረሰቡን ህይወት የሚለውጡ ስራዎች መስራቱን አብራርተዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026