የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በክልሉ የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት የሚያሳድጉ የግብርና ግብዓቶች እየቀረቡ ነው

May 19, 2025

IDOPRESS

ቡኖ በደሌ፤ ግንቦት 9/2017(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በመኸር ወቅት የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት የሚያሳድጉ የግብርና ግብዓቶች እየቀረቡ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

የክልሉ ግብርና ቢሮ የስራ ሀላፊዎች በቡኖ በደሌ ዞን የመኸር እርሻ እንቅስቃሴን ተመልክተዋል።

በዚሁ ጊዜ የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ በሪሶ ፈይሳ እንደገለጹት በክልሉ በመኸር እርሻ ምርትና ምርታማነትን ለማሳድግ ግብዓት በስፋት እየቀረበ ነው።

በክልሉ በዘንድሮ የመኸር እርሻ 10 ነጥብ 8 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን ታቅዶ አስፈላጊ ግብዓቶች እየቀረቡ መሆኑን ተናግረዋል።

ለመኸር አዝመራ ከሚያስፈለገው የአፈር ማዳበሪያ ውስጥ እስካሁን ከስድስት ሚሊዮን በላይ የሚሆነው ወደ ክልሉ መድረሱን ገልጸው ከዚህ ውስጥ 1 ነጥብ 6 ሚሊዮን የሚሆነው አርሶ አደሩ እጅ ደርሷል ብለዋል።

በሌላ በኩል በክልሉ በአፈር አሲዳማነት የተጠቃ መሬትን በተፈጥሮ ማዳበሪያ ለማከም አበረታች ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።


በክልሉ ቡኖ በደሌ ዞን ዳቦ ሃና ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር አሸናፊ ጸጋዬ፤ ለመኸር እርሻ መሬታቸውን በትራክተር በማረስ እያዘጋጁ መሆኑን ተናግረዋል።

በጋ ላይ ስንዴ በክላስተር አርሰው የተሻለ ምርት ያገኙበት ማሳቸውን አሁን ደግሞ በመኸር እርሻ በቆሎ ለማልማት እየተዘጋጁ መሆኑን ገልጸዋል።


ሌላው አርሶ አደር ኦበሳ ዳባሳ፤ በአቅራቢያቸው ካሉ ሌሎች አርሶ አደሮች ጋር በመሆን መሬታቸውን በክላስተር ለማልማት እያረሱና ለመዝራት እየተዘጋጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ተቀናጅተን በክላስተር ማልማታችን የተሻለ ምርት ለማግኘት ያስችለናል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.