
ቡኖ በደሌ፤ ግንቦት 9/2017(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በመኸር ወቅት የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት የሚያሳድጉ የግብርና ግብዓቶች እየቀረቡ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
የክልሉ ግብርና ቢሮ የስራ ሀላፊዎች በቡኖ በደሌ ዞን የመኸር እርሻ እንቅስቃሴን ተመልክተዋል።
በዚሁ ጊዜ የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ በሪሶ ፈይሳ እንደገለጹት በክልሉ በመኸር እርሻ ምርትና ምርታማነትን ለማሳድግ ግብዓት በስፋት እየቀረበ ነው።
በክልሉ በዘንድሮ የመኸር እርሻ 10 ነጥብ 8 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን ታቅዶ አስፈላጊ ግብዓቶች እየቀረቡ መሆኑን ተናግረዋል።
ለመኸር አዝመራ ከሚያስፈለገው የአፈር ማዳበሪያ ውስጥ እስካሁን ከስድስት ሚሊዮን በላይ የሚሆነው ወደ ክልሉ መድረሱን ገልጸው ከዚህ ውስጥ 1 ነጥብ 6 ሚሊዮን የሚሆነው አርሶ አደሩ እጅ ደርሷል ብለዋል።
በሌላ በኩል በክልሉ በአፈር አሲዳማነት የተጠቃ መሬትን በተፈጥሮ ማዳበሪያ ለማከም አበረታች ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።

በክልሉ ቡኖ በደሌ ዞን ዳቦ ሃና ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር አሸናፊ ጸጋዬ፤ ለመኸር እርሻ መሬታቸውን በትራክተር በማረስ እያዘጋጁ መሆኑን ተናግረዋል።
በጋ ላይ ስንዴ በክላስተር አርሰው የተሻለ ምርት ያገኙበት ማሳቸውን አሁን ደግሞ በመኸር እርሻ በቆሎ ለማልማት እየተዘጋጁ መሆኑን ገልጸዋል።

ሌላው አርሶ አደር ኦበሳ ዳባሳ፤ በአቅራቢያቸው ካሉ ሌሎች አርሶ አደሮች ጋር በመሆን መሬታቸውን በክላስተር ለማልማት እያረሱና ለመዝራት እየተዘጋጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ተቀናጅተን በክላስተር ማልማታችን የተሻለ ምርት ለማግኘት ያስችለናል ብለዋል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025