
ቡኖ በደሌ፤ ግንቦት 9/2017(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በመኸር ወቅት የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት የሚያሳድጉ የግብርና ግብዓቶች እየቀረቡ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
የክልሉ ግብርና ቢሮ የስራ ሀላፊዎች በቡኖ በደሌ ዞን የመኸር እርሻ እንቅስቃሴን ተመልክተዋል።
በዚሁ ጊዜ የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ በሪሶ ፈይሳ እንደገለጹት በክልሉ በመኸር እርሻ ምርትና ምርታማነትን ለማሳድግ ግብዓት በስፋት እየቀረበ ነው።
በክልሉ በዘንድሮ የመኸር እርሻ 10 ነጥብ 8 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን ታቅዶ አስፈላጊ ግብዓቶች እየቀረቡ መሆኑን ተናግረዋል።
ለመኸር አዝመራ ከሚያስፈለገው የአፈር ማዳበሪያ ውስጥ እስካሁን ከስድስት ሚሊዮን በላይ የሚሆነው ወደ ክልሉ መድረሱን ገልጸው ከዚህ ውስጥ 1 ነጥብ 6 ሚሊዮን የሚሆነው አርሶ አደሩ እጅ ደርሷል ብለዋል።
በሌላ በኩል በክልሉ በአፈር አሲዳማነት የተጠቃ መሬትን በተፈጥሮ ማዳበሪያ ለማከም አበረታች ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።

በክልሉ ቡኖ በደሌ ዞን ዳቦ ሃና ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር አሸናፊ ጸጋዬ፤ ለመኸር እርሻ መሬታቸውን በትራክተር በማረስ እያዘጋጁ መሆኑን ተናግረዋል።
በጋ ላይ ስንዴ በክላስተር አርሰው የተሻለ ምርት ያገኙበት ማሳቸውን አሁን ደግሞ በመኸር እርሻ በቆሎ ለማልማት እየተዘጋጁ መሆኑን ገልጸዋል።

ሌላው አርሶ አደር ኦበሳ ዳባሳ፤ በአቅራቢያቸው ካሉ ሌሎች አርሶ አደሮች ጋር በመሆን መሬታቸውን በክላስተር ለማልማት እያረሱና ለመዝራት እየተዘጋጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ተቀናጅተን በክላስተር ማልማታችን የተሻለ ምርት ለማግኘት ያስችለናል ብለዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026