
አዲስ አበባ፤ግንቦት 10/2017 (ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ ተገንብተው ለአገልግሎት ክፍት የተደረጉ የኮሪደር ልማት ስፍራዎች ለወጣቱ አማራጭ የመዝናኛ ስፍራ ሆነው እያገለገሉ እንደሚገኙ ኢዜአ ያነጋገራቸው ወጣቶች ገለፁ።
በአዲስ አበባ ተገንብተው ለአገልግሎት የበቁና በግንባታ ሂደት የሚገኙ የኮሪደር ልማትና የመልሶ ግንባታ ተግባራት መዲናዋን ውብ ገጽታ በማላበስ ለነዋሪዎቿ ምቹ የኑሮ ምኅዳርን ፈጥረዋል።
አዲስ አበባ በዓለም አቀፍ ደረጃ የከተማ ተወዳዳሪነት አቅምን በመፍጠር ከኢትዮጵዊያን ባሻገር የአፍሪካ መዲናነቷን እንድታስጠብቅ ወሳኝ ዕድል ፈጥሮላታል።
በአዲስ አበባ ከተማ ተገንብተው ለአገልግሎት የበቁና በግንባታ ሂደት የሚገኙ የኮሪደር ልማትና የመልሶ ግንባታ ተግባራት አስመልክቶም ኢዜአ ያነጋገራቸው የመዲናዋ ወጣቶች አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
አስተያየት ሰጪዎቹም፤ መዲናዋን ውብ ገጽታ ያላበሷትና ምቹ የከተሜነት ምኅዳር እያጎናጸፏት የሚገኙ የኮሪደርና መልሶ ግንባታ ስራዎች የወጣቱን ፍላጎትና መሻት ታሳቢ ያደረጉ ናቸው።
ወጣት እስራኤል ዳንኤል እንደሚለውም፤ በካዛንችስና አካባቢው በአጭር ጊዜ ውስጥ ፍጥነትን ከጥራት ያዋሃዱ አኩሪ የልማት ስራዎች መሰራታቸውን ታዝቧል።
በአጭር ጊዜ በጥራትና ፍጥነት ተገንብተው ለአገልግሎት የበቁ ፕሮጀክቶችም አካባቢውን ወብ ገጽታ በማላበስ ለመዲናዋ ነዋሪዎች ማራኪና አማራጭ የመዝናኛ ቦታ መፍጠራቸውን ተናግሯል።
መዲናዋን ውብ ገጽታ ያላበሷት የኮሪደር ልማት ስራዎችን መጎብኘት በስራ የደከመን መንፈስ የሚያበረቱ ናቸው ያለው ደግሞ ከሳሪስ አካባቢ ለመዝናናት እንደመጣ የገለጸው ወጣት ደሳለኝ ይፍረደው ነው።
በብዙ መልኩ ውብ ገጽታን የተላበሱት የካዛንችስና አቧሬ አካባቢዎችም የነበራቸውን የደበዘዘ ገጽታ በመቀየር ለመዲናዋ ወጣቶች በአማራጭ የመዝናኛ ስፋራነት እያገለገሏቸው እንደሚገኝ ገልጿል።
አቧሬ አካባቢ እንደምትኖር የገለጸችው ሶፍያ መሃመድም እንዲሁ፤ የካዛንችስ ኮሪደር ልማት በጥራትና ፍጥነት ተጠናቆ ለአገልግሎት መብቃቱ አግራሞትን ፈጥሮብኛል ብላለች።
በአካባቢው የተደረገው ውብና ማራኪ የልማት ስራም ህፃናት እንዳሻቸው ቦርቀው እንዲጫዎቱ፤ ወጣችም ሃሳባቸውን በጥሞና እንዲቀያየሩ ዕድል መፍጠሩን ተናግረዋል።
እንደ ወይዘሮ ዘነበች አተዎ ገለፃ፤ በካዛንችስና አካባቢው የተደረገው ሁለንተናዊ ለውጥ ማራኪ ስፋራን በመፍጠር ለመዲናዋ ወጣቶች ድንቅ የመዝናኛ ቦታ ለመሆን ችሏል።
አስተያየት ሰጪዎቹ አክለውም ከተማዋን ውብ ገጽታ ያላበሷት የልማት ፕሮጀክቶች የመዲናዋን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት በማሳደግ ለነዋሪዎች ምቹ የኑሮ ከባቢ መፈጠሩን አንስተዋል።
የመዲናዋ ነዋሪዎችም በጥራትና ፍጥነት ተገንብተው ለአገልግሎት የበቁ ማራኪ የኮሪደር ልማት ስራዎችን በመጠበቅና በመንከባከብ ለቀጣዩ ትውልድ ማስተላለፍ እንደሚገባ ነው አጽንኦት የሰጡት።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025