
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 12/2017(ኢዜአ)፦ ፋይዳ የዲጂታል መታወቂያ ለኢትዮጵያ የሁሉን አቀፍ ዕድገትና የዘመናዊነት ጉዞ ስኬት ሁነኛ ማሳያ መሆኑን የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ዋና ዳይሬክተር ዮዳሔ አርአያሥላሴ ገለጹ፡፡
ዲጂታል ማንነት ላይ ያተኮረው አይዲ 4 አፍሪካ ዓመታዊ ጉባዔ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እንዲሁም ከፍተኛ የመንግሥት አመራሮች፣ ከ105 ሀገራት የመጡ ተወካዮችን ጨምሮ ከ2 ሺህ በላይ ተሳታፊዎች በተገኙበት በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል።

በጉባኤው ኢትዮጵያ ብሔራዊ የዲጂታል መታወቂያ ወይም ፋይዳ ስርዓትን በስኬታማነት ተግባራዊ እያደረገች መሆኗ ተገልጿል።
ፋይዳ ለኢትዮጵያ የዲጂታላይዜሽን ጉዞ ወሳኝ የሆነ የዲጂታል መሰረተ ልማት መገንባት ላይ ያተኮረ ነውም ተብሏል፡፡
የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ዋና ዳይሬክተር ዮዳሔ አርአያሥላሴ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፤ 15 ሚሊየን ዜጎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤት መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
ፋይዳ ዲጂታል ኢትዮጵያን የመገንባት ጉዞ አካል መሆኑን አንስተው ለኢትዮጵያ መጻኢ ዕድል መሠረት ስለመሆኑም ተናግረዋል፡፡
ኢትዮጵያ በፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ እያስመዘገበች ለምትገኘው ስኬት የመንግሥት ቁርጠኝነት፣ ብቃት ያላቸው ባለሙያዎች እንዲሁም የባለድርሻ አካላት ሚና ከፍተኛ ነው ብለዋል፡፡
ፋይዳ የዲጂታል መታወቂያ ኢትዮጵያ እያደረገች ለምትገኘው ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን መሳካት ጉልህ አበርክቶ እንዳለውም ተናግረዋል፡፡
ለኢትዮጵያ ሁሉን አቀፍ ዕድገትና የዘመናዊነት ጉዞ ስኬት ቁርጠኝነት ማሳያ መሆኑንም ጨምረው ጠቁመዋል፡፡
የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ስርዓት ተግባራዊ በሆነባቸው ተቋማት አገልግሎት ለመስጠት ይወስድ የነበረውን ጊዜ እስከ 60 በመቶ መቀነስ ማስቻሉን ተናግረዋል፡፡
የዲጂታል መታወቂያው በመንግስትም ይሁን በግል ተቋማት ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት እንዲሁም ለተደራሽነት ትልቅ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝም ገልጸዋል፡፡
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026