የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በኢትዮጵያ ተግባራዊ የተደረጉ የልማት ኢኒሼቲቮች የኢኮኖሚ ዕድገቱን ከማሳለጥ ባለፈ ለሥራ ዕድል ፈጠራ ጉልህ ሚና እየተጫወቱ ነው - ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ(ዶ/ር)

May 21, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2017(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ተግባራዊ የተደረጉ የልማት ኢኒሼቲቮች የኢኮኖሚ ዕድገቱን ከማሳለጥ ባለፈ ለሥራ ዕድል ፈጠራ ጉልህ ሚና እየተጫወቱ መሆኑን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ(ዶ/ር) ተናገሩ።

20ኛው የዓለም ሥራ ድርጅት በሥራ ላይ የተመሰረተ የባለሙያዎች አህጉራዊ ስብሰባ "የማይበገር ማህበረሰብ እና ጤናማ አካባቢ የሰው ኃይልን በብዛት የሚጠቀሙ የኢንቨስትመንት ፕሮግራም አካሄዶች" በሚል መሪ ሀሳብ በአፍሪካ ሕብረት መሰብሰቢያ አዳራሽ እየተካሄደ ነው።

በስብሰባው የመንግስት ከፍተኛ የሥራ ሀላፊዎች፣ የተለያዩ ሀገራት ተወካዮች፣ የዓለም አቀፍ ተቋማት መሪዎች ተገኝተዋል።

ከስብሰባው ጎን ለጎንም ሀገራት በሥራ ዕድል ፈጠራ ዙሪያ ያላቸውን ተሞክሮ የሚለዋወጡበት የፓናል ውይይት ተካሂዷል።

የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ አካታች የኢኮኖሚ ሥርዓት በመዘርጋትና በሥራ ዕድል ፈጠራ ረገድ ስኬታማ ተግባራት እየተከናወኑ ናቸው።

የግሉ ክፍለ ኢኮኖሚ ለስራ ዕድል ፈጠራው ያለውን ጉልህ ሚና በማጤንም መንግሥት የግሉን ዘርፍ በማበረታታት ሰፊ የሥራ ዕድል እንዲፈጥር ሁኔታዎችን ማመቻቸቱንም ጠቅሰዋል።

ከዚህ ቀደም በአመዛኙ በግብርና ላይ የተመሰረተ የሥራ ዕድል ፈጠራ እንደነበር አስታውሰው፤ የብዝሃ ኢኮኖሚ አሰራርን በመከተል ከግብርና ባሻገር በአምራች ኢንዱስትሪ፣ በማዕድን፣ በቱሪዝም እንዲሁም በዲጂታል ኢኮኖሚ የሥራ ዕድል ፈጠራውን የሚያሳልጡ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።

በሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ መርሃ ግብርም የሥራ ዕድል ፈጠራ ጉዳይ ኢትዮጵያ ቁልፍ አጀንዳ ማድረጓን ገልጸው፤ ይህም የሥራ ዕድል ፈጠራ እንቅስቃሴው ላይ አበረታች ውጤቶች እንዲገኙ እያደረገ መሆኑን አብራርተዋል።

በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለዜጎች የስራ እድል መፈጠሩን ለአብነት ጠቅሰው፤ የኮሪደር ልማትን ጨምሮ በግንባታው መስክ የተገኘው ውጤት ተጠቃሽ መሆኑን አስረድተዋል።

በሀገሪቱ ወደ ሥራ የገቡት የኢንዱስትሪ ፓርኮች እና ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖችም ለበርካታ ዜጎች የሥራ እድል ፈጥረዋል ነው ያሉት።

የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ደኤታ ተሻለ በሬቻ(ዶ/ር) በበኩላቸው እንደተናገሩት፤ በሴፍቲኔት መርሃ ግብር በገጠርና በከተማ የሥራ ዕድል ዜጎች ተጠቃሚ እየሆኑ ነው።

ክህሎት መር ፖሊሲ አሰራርን በመተግበርም የተቋማት ፍላጎትን መሰረት ያደረገ የሰለጠነ የሰው ኃይል ወደ ሥራ እንዲገባ የተጀመሩ እንቅስቃሴዎች ፍሬ እያፈሩ መሆኑንም አንስተዋል።

በተለይም በዲጂታል መስክ ስታርታፖችን በመደገፍ የሥራ ዕድል እንዲፈጥሩ በተዘረጋው ማበረታቻ ሥርዓት በርካታ ስታርታፖች ምህዳሩን እየተቀላቀሉ ነው ብለዋል።

በክህሎት ልማት ዘርፍ ቀጣናዊ ትብብሮችን በማጠናከር ለጋራ ብልጽግና ትኩረት ተሰጥቷል ሲሉም ተናግረዋል።

በዓለም የሥራ ድርጅት የልማትና ኢንቨስትመንት ቅርንጫፍ የቅጥር ፖሊሲ መምሪያ ኃላፊ ሚቶ ቱስካማቶ እንዳሉት፤ እያደገ የመጣው የመሰረተ ልማት ግንባታ ተገቢው የሥራ ዕድል እንዲፈጥር ሀገራት የተሻለ አሰራር ቀርጸው ሊንቀሳቀሱ ይገባል።

በሥራ ዕድል ፈጠራ ዙሪያ ያሉ መልካም ተሞክሮዎችን በመለዋወጥ በተለይም ተጋላጭ የሆኑ የኀብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ማድረግ ላይ ርብርብ ይጠይቃል ነው ያሉት።

ስብሰባውን የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከዓለም የሥራ ድርጅት(ILO) ጋር በመተባበር ያዘጋጁት ሲሆን፤ ከግንቦት 11 እስከ 15 ቀን 2017 ዓ.ም ይቆያል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026