አዲስ አበባ፤ግንቦት 18/2017(ኢዜአ)፦በመጪው ክረምት በሚኖራቸው የእረፍት ጊዜ የኮደርስ ስልጠናን በመከታተል የዲጂታል ክህሎታቸውን ለማሳደግ ዝግጁ መሆናቸውን የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች ገለፁ።
የአዲስ አበባ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ አዋሌ መሀመድ በበኩላቸው እስካሁን 130 ሺህ ዜጎች የኮደርስ ስልጠና ማጠናቀቃቸውን ተናግረዋል።
የ5 ሚሊየን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ የስልጠና ተነሳሽነት "ትውልድ ይማር፣ትውልድ ይሰልጥን፣ከዓለም ጋር ይፎካከር" በሚል እሳቤ ዲጅታል ክህሎትን የተላበሰ ብቁ ዜጋ ለማፍራት እየተተገበረ ይገኛል፡፡
ተነሳሽነቱ በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት ዜጎች በዌብ ፕሮግራሚንግ፣ በአንድሮይድ ማበልፀግ፣ዳታ ሳይንስና አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ መሠረታዊ የዲጂታል እውቀት እንዲጨብጡ የሚያስችል ነው።
በኮከበ ፅባህ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤትና በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የሳይንስ ሼርድ ካምፓስ የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች ለኢዜአ እንዳሉት የኮደርስ ስልጠና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን የሚያሳድግ ነው።
ተማሪ አቤኔዘር ዘገየወርቅ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በሰመር ካምፕ የኮደርስ ስልጠና በመከታተል የምስክር ወረቀት ማግኘቱን ተናግሯል።
የኮደርስ ስልጠናን እየተከታተለ እንደሚገኝ የጠቀሰው ተማሪ አብርሃም ሰላምነህ በበኩሉ፥ ስልጠናው የተለያዩ የትምህርት እድሎችን ለማግኘት ጠቀሜታ እንደሚኖረው ገልጿል።
ስልጠናው ዓለም አቀፍ እውቅና ማግኘት የሚያስችል፣ ተወዳዳሪነትን የሚያሳድግና ተጨማሪ እድሎችን የሚከፍት በመሆኑ በእረፍት ጊዜው ለመከታተል ዝግጁ መሆኑን የገለፀው ደግሞ ተማሪ ባሴል ደረጀ ነው።
ተማሪ አማኑኤል ታሪኩ በበኩሉ ከፈተና በኃላ በሚኖረው የእረፍት ጊዜ ወደቀጣይ ምዕራፍ የሚያሸጋግሩ ተግባራትን ለማከናወን እንዳሰበ ገልጾ የኮደርስ ስልጠና የዕቅዱ አካል መሆኑን ተናግሯል።
ተማሪዎች በመጪው ክረምት የእረፍት ጊዜያቸውን ስልጠናውን በመከታተል ራሳቸውን ማብቃት ይገባል ያለችው ደግሞ ተማሪ ኮሊያ ገረመው ናት።
በኮደርስ ስልጠና የተካተቱ ኮርሶች ለመጪው ዘመን አስፈላጊ እውቀት የሚያስጨብጡ በመሆናቸው በእረፍት ጊዜ ክህሎትን ማዳበር እንደሚገባ ተማሪ ሰሎሜ ታደሰ ገልጻለች።
የአዲስ አበባ ከተማ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ አዋሌ መሀመድ እንዳሉት፥ የኮደርስ ስልጠና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትና ተጠቃሚነትን የሚያጎለብት እንዲሁም ፈጠራና ስታርትአፕን የሚያበረታታ ነው።
በመዲናዋ እስካሁን 218 ሺህ በላይ ዜጎች የኮደርስ ስልጠናን እየተከታተሉ መሆናቸውን ጠቅሰው፥ 130 ሺህ ያህሉ ማጠናቀቃቸውንም አንስተዋል።
በቀጣይም በኮሌጆች፣ በመንግስት መስሪያ ቤቶች፣ በቴክኒክና ሙያ ኮሌጆችና በክረምቱ ወቅት ደግሞ የ12ተኛ ክፍል ተማሪዎች ስልጠናውን እንዲከታተሉ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025
ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...
Feb 8, 2025