
ባህር ዳር፤ ግንቦት 19/2017(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በጀትን ለታለመለት ዓላማ እንዲውል በሚደረገው ጥረት የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ ሚና መጠናከር እንዳለበት የክልሉ ገንዘብ ቢሮ ገለጸ።
ቢሮው በመንግስት የፋይናንስ አስተዳደርና በፋይናንስ ግልፀኝነትና ተጠያቂነት ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ለሚዲያና ኮሙኒኬሽን አመራሮችና ባለሙያዎች ዛሬ ሰጥቷል።
የቢሮው ኃላፊ ጥላሁን መኃሪ(ዶ/ር) በመድረኩ እንደገለፁት በክልሉ የተመደበውን በጀት ለታለመለት ዓላማ መዋል አለመዋሉን ለመቆጣጠር በሚደረገው ጥረት የመገናኛ ብዙሃንና የኮሙኒኬሽን ዘርፉ ሚና ሊጠናከር እንደሚገባ ተናግረዋል።

ይህም ውስን የሆነውን የህዝብ ሃብት ለክልሉ እድገት በማዋል የህብረተሰቡን ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ አስፈላጊ መሆኑን ነው የገለጹት።
በክልሉ የሚበጀተውን በጀት ህብረተሰቡ የማወቅ መብት አለው ያሉት የቢሮ ኃላፊው የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉም የፋይናንስ ግልፅነትና ተጠያቂነትን በማረጋገጥ ኃላፊነቱን ሊያጠናክር ይገባል ብለዋል።

በመድረኩ የተሳተፉት የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን የኮርፖሬት ዘርፍ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አስቻለ አየሁዓለም እንደገለጹት በጀት የልማት ስራዎች ማሳለጫ ቁልፍ መሳሪያ ነው።
ለልማቱ የሚመደብን ውስን በጀት ለታለመለት ተግባር እንዲውል የፋይናንስ ግልፀኝነትና ተጠያቂነት እንዲረጋገጥ ህብረተሰቡን የማስገንዘብና የማሳወቅ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
አሚኮ በጉዳዩ ላይ የህብረተሰቡን ግንዛቤ በማሳደግ በኩል የሚሰራውን ስራ አጠናክሮ እንደሚያስቀጥልም አረጋግጠዋል።

የክልሉ መንገድ ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ በትግሉ ተስፋሁን በበኩላቸው በመድረኩ ስለፋይናንስ ግልፀኝነትና ተጠያቂነት በቂ ግንዛቤ ማግኘታቸውን ተናግረዋል።
ያገኙትን ግንዛቤም በተቋማቸው የሚከናወኑ የመንገድ ፕሮጀክቶች የፋይናንስ ግልፀኝነትና ተጠያቂነት ባረጋገጠ መልኩ እንዲከናወኑ የድርሻቸውን እንዲወጡ የሚያስችል መሆኑን አስረድተዋል።
ለአንድ ቀን በተዘጋጀው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናም ከክልሉ ቢሮዎችና ከተለያዩ የሚዲያ አካላት የተውጣጡ የስራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026