
ጋምቤላ ፤ግንቦት 20/2017 (ኢዜአ)፡- የዲጂታል መሰረተ ልማትና የሰው ኃይል ልማትን በማጠናከር የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታን ለማፋጠን የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ (ዶ/ር) ገለጹ።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ (ዶ/ር) ከጋምቤላ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር) ጋር በመሆን በክልሉ ርዕሰ መስተዳደር ጽህፈት ቤት የተገነባውን የስማርት ኮሙኒኬሽን ክፍል መርቀዋል።

ሚኒስትር ዴኤታው በዚሁ ወቅት እንደገለጹት የዲጂታል መሰረተ ልማት እንደ ሀገር ለታለመው የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።
የዲጂታል መሰረተ ልማት በተለይም የሰው ኃይል ልማቱን በማሳለጥ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን ለማሳደግ ዓይነተኛ ፋይዳ ያለው መሆኑን አንስተዋል።
በመሆኑም የዲጂታል መሰረተ ልማትና የሰው ኃይል ልማትን በማጠናከር የኢትዮጵያን የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ለማፋጠን የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።
የስማርት ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂው የጤና፣ የትምህርትና ሌሎች የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን ወጪና ጊዜ ቆጣቢ በሆነ መንገድ ለማሳለጥ የሚያስችል ስለመሆኑም አስረድተዋል።
ሚኒስቴሩ ከክልሎች ጋር በመተባበር በዕለቱ የተመረቀውን የዲጂታል ኮሙኒኬሽን ስማርት ክፍል ያስገነባው የክልሎችን ፍትሐዊ ተጠቀሚነት ለማረጋገጥ በማለም መሆኑንም ገልጸዋል።

የጋምቤላ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር) በበኩላቸው የዲጂታል መሰረተ ልማት የታለመውን የልማትና የብልጽግና ጉዞ ለማሳለጥ የጎላ ጠቀሜታ አለው ብለዋል።
የዲጅታል መሰረተ ልማት እየተካሄዱ ለሚገኙት የማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና የዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ መሳለጥ የጎላ አበርክቶ እንዳለው አንስተው የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር በክልሉ ላስገነባው የስማርት ኮሙኒኬሽን መሰረተ ልማት አመስግነዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026