የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የዲጂታል መሰረተ ልማትና የሰው ኃይል ልማትን በማጠናከር የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታን ለማፋጠን የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ነው

May 30, 2025

IDOPRESS

ጋምቤላ ፤ግንቦት 20/2017 (ኢዜአ)፡- የዲጂታል መሰረተ ልማትና የሰው ኃይል ልማትን በማጠናከር የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታን ለማፋጠን የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ (ዶ/ር) ገለጹ።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ (ዶ/ር) ከጋምቤላ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር) ጋር በመሆን በክልሉ ርዕሰ መስተዳደር ጽህፈት ቤት የተገነባውን የስማርት ኮሙኒኬሽን ክፍል መርቀዋል።


ሚኒስትር ዴኤታው በዚሁ ወቅት እንደገለጹት የዲጂታል መሰረተ ልማት እንደ ሀገር ለታለመው የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።

የዲጂታል መሰረተ ልማት በተለይም የሰው ኃይል ልማቱን በማሳለጥ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን ለማሳደግ ዓይነተኛ ፋይዳ ያለው መሆኑን አንስተዋል።

በመሆኑም የዲጂታል መሰረተ ልማትና የሰው ኃይል ልማትን በማጠናከር የኢትዮጵያን የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ለማፋጠን የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።

የስማርት ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂው የጤና፣ የትምህርትና ሌሎች የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን ወጪና ጊዜ ቆጣቢ በሆነ መንገድ ለማሳለጥ የሚያስችል ስለመሆኑም አስረድተዋል።

ሚኒስቴሩ ከክልሎች ጋር በመተባበር በዕለቱ የተመረቀውን የዲጂታል ኮሙኒኬሽን ስማርት ክፍል ያስገነባው የክልሎችን ፍትሐዊ ተጠቀሚነት ለማረጋገጥ በማለም መሆኑንም ገልጸዋል።


የጋምቤላ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር) በበኩላቸው የዲጂታል መሰረተ ልማት የታለመውን የልማትና የብልጽግና ጉዞ ለማሳለጥ የጎላ ጠቀሜታ አለው ብለዋል።

የዲጅታል መሰረተ ልማት እየተካሄዱ ለሚገኙት የማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና የዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ መሳለጥ የጎላ አበርክቶ እንዳለው አንስተው የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር በክልሉ ላስገነባው የስማርት ኮሙኒኬሽን መሰረተ ልማት አመስግነዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026