
ባህርዳር ፤ ግንቦት 22/2017 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል በእርሻ ኢንቨስትመንት ለሚሰማሩ ባለሃብቶች 11ሺህ 267 ሄክታር መሬት ተለይቶ መዘጋጀቱን የክልሉ መሬት ቢሮ አስታወቀ።
በቢሮው የገጠር መሬት ኢንቨስትመንት ዳይሬክተር አቶ ጥጋቡ በላይ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በክልሉ በእርሻ ኢንቨስትመንት ዘርፍ ለሚሰማሩ ባለሃብቶች መሬት ተለይቶ የተዘጋጀው በ10 ዞኖች ውስጥ ነው።
ለእርሻ ኢንቨስትመንት እንዲውል ተለይቶ ከተዘጋጀው 11 ሺህ 267 መሬት ከ2 ሺህ ሄክታር የሚበልጠው ቀደም ሲል የመስሪያ ቦታ ጠይቀው ሲጠባበቁ ለቆዩ 20 ባለሃብቶች መተላለፉን ተናግረዋል።

እነዚሀ ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ በመውሰድ እያንዳንዳቸው ከ20 እስከ 100 ሚሊዮን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ መሆናቸውን አመልክተዋል።
ቀሪው ከዘጠኝ ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በቀጣይ ለሚቀርቡ ባለሃብቶች ለማስተላለፍም አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጓል ብለዋል።
ባለሃብቶቹ የሚያቀርቡት የኢንቨስትመንት ፕሮጀክት ተገምግሞ አሸናፊ ለሚሆኑት መሬቱን ፈጥኖ በማስረከብ ወደልማት እንዲገቡ ድጋፍና ክትትል እንደሚደረግ ገልጸዋል።
ባለሃብቶቹ ወደስራ ሲሰማሩም ለበርካታ ዜጎች የስራ ዕድል እንደሚፈጥሩም አቶ ጥጋቡ አስታውቀዋል።
በአማራ ክልል ኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን በእርሻ ኢንቨስትመንት ዘርፍ የተሰማሩት አቶ መስፍን ክፍሉ በሰጡት አስተያየት፤ በወሰዱት መሬት ላይ እያለሙ መሆኑን ገልጸዋል።
ይህም በ2017/2018 የምርት ዘመንም የበቆሎ ዘር ለማባዛት በአሁኑ ወቅት መሬቱን አለስልሰው ማጠናቀቃቸውን ጠቅሰዋል።
ቀደም ሲልም በተለይ ለአካባቢው አርሶ አደር የዕውቀትና የቴክኖሎጂ ሽግግር በማድረግ በቆሎ፣ ማሽላ፣ ማሾ፣ ቲማቲምና ሽንኩርት በማልማት ውጤታማ እንደሆኑም አውስተዋል።
ለበርካታ ዜጎችም የስራ ዕድል መፍጠራቸውን ጠቁመዋል።
ባለፉት ዓመታት በክልሉ በእርሻ ኢንቨስትመንት የተሰማሩ አንድ ሺህ 638 ባለሃብቶች በተረከቡት 203 ሺህ 858 ሄክታር መሬት ላይ እያለሙ መሆኑን ከቢሮው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025