
ባህርዳር ፤ ግንቦት 22/2017 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል በእርሻ ኢንቨስትመንት ለሚሰማሩ ባለሃብቶች 11ሺህ 267 ሄክታር መሬት ተለይቶ መዘጋጀቱን የክልሉ መሬት ቢሮ አስታወቀ።
በቢሮው የገጠር መሬት ኢንቨስትመንት ዳይሬክተር አቶ ጥጋቡ በላይ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በክልሉ በእርሻ ኢንቨስትመንት ዘርፍ ለሚሰማሩ ባለሃብቶች መሬት ተለይቶ የተዘጋጀው በ10 ዞኖች ውስጥ ነው።
ለእርሻ ኢንቨስትመንት እንዲውል ተለይቶ ከተዘጋጀው 11 ሺህ 267 መሬት ከ2 ሺህ ሄክታር የሚበልጠው ቀደም ሲል የመስሪያ ቦታ ጠይቀው ሲጠባበቁ ለቆዩ 20 ባለሃብቶች መተላለፉን ተናግረዋል።

እነዚሀ ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ በመውሰድ እያንዳንዳቸው ከ20 እስከ 100 ሚሊዮን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ መሆናቸውን አመልክተዋል።
ቀሪው ከዘጠኝ ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በቀጣይ ለሚቀርቡ ባለሃብቶች ለማስተላለፍም አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጓል ብለዋል።
ባለሃብቶቹ የሚያቀርቡት የኢንቨስትመንት ፕሮጀክት ተገምግሞ አሸናፊ ለሚሆኑት መሬቱን ፈጥኖ በማስረከብ ወደልማት እንዲገቡ ድጋፍና ክትትል እንደሚደረግ ገልጸዋል።
ባለሃብቶቹ ወደስራ ሲሰማሩም ለበርካታ ዜጎች የስራ ዕድል እንደሚፈጥሩም አቶ ጥጋቡ አስታውቀዋል።
በአማራ ክልል ኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን በእርሻ ኢንቨስትመንት ዘርፍ የተሰማሩት አቶ መስፍን ክፍሉ በሰጡት አስተያየት፤ በወሰዱት መሬት ላይ እያለሙ መሆኑን ገልጸዋል።
ይህም በ2017/2018 የምርት ዘመንም የበቆሎ ዘር ለማባዛት በአሁኑ ወቅት መሬቱን አለስልሰው ማጠናቀቃቸውን ጠቅሰዋል።
ቀደም ሲልም በተለይ ለአካባቢው አርሶ አደር የዕውቀትና የቴክኖሎጂ ሽግግር በማድረግ በቆሎ፣ ማሽላ፣ ማሾ፣ ቲማቲምና ሽንኩርት በማልማት ውጤታማ እንደሆኑም አውስተዋል።
ለበርካታ ዜጎችም የስራ ዕድል መፍጠራቸውን ጠቁመዋል።
ባለፉት ዓመታት በክልሉ በእርሻ ኢንቨስትመንት የተሰማሩ አንድ ሺህ 638 ባለሃብቶች በተረከቡት 203 ሺህ 858 ሄክታር መሬት ላይ እያለሙ መሆኑን ከቢሮው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...
Aug 28, 2026
መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...
Aug 18, 2026
ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...
Aug 10, 2026
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...
Jul 20, 2026