
አርባ ምንጭ፤ ግንቦት 25/2017(ኢዜአ)፦ በየደረጃው ያለው አመራር ለህዝብ ጥያቄዎች ወቅቱን የዋጀ ምላሽ ለመስጠት በአመራር ጥበብ መታገዝ እንዳለበት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ።
በፐብሊክ ኢንተርፕርነርሽፕ እና ኢኖቬሽን ስነ-ምህዳር ግንባታ ላይ ያተኮረ ስልጠና ለክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በአርባ ምንጭ ከተማ ዛሬ መሰጠት ተጀምሯል።
በመድረኩ መልዕክት ያስተላለፉት ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ አመራሩ እያደገ ለመጣው የህዝብ ተለዋዋጭ ጥያቄ ወቅቱን የዋጀ ምላሽ ለመስጠት በአመራር ጥበብ ታግዞ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት ገልጸዋል።
የክልሉን ሁለንተናዊ ዕድገት ለማረጋገጥ ከመቼውም ጊዜ በላይ አመራሩ በቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባውም አመልክተዋል።

የለውጡ መንግስት ዘመኑን በሚዋጅ እይታ በመንቀሳቀስና ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር በሁለንተናዊ የልማት ዘርፎች ውጤት እያስመዘገበ ይገኛል ሲሉም አክለዋል።
እየተስተዋሉ ላሉ ተደራራቢና ተለዋዋጭ ክስተቶች ተገቢ ምላሽ ለመስጠት መንግስት ፈጠራና ፍጥነት የታከለበት ተግባር እያከናወነ ይገኛል ብለዋል።
ክልሉን የሰላም፣ የመቻቻልና የብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ ከተለመደው አሰራር በመውጣት በፈጠራና በፍጥነት የታከለ የኢንተርፕርነርሽፕ እና ኢኖቬሽን ስነ-ምህዳር ለመፍጠር እንደሚሰራም ተናግረዋል።

የፌዴራል ኢንተርፕሪነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ሀሰን ሁሴን(ዶ/ር) እንዳሉት የፐብሊክ ኢንተርፕርነርሽፕ እና ኢኖቬሽን ስነ-ምህዳር ግንባታ ላይ ለአመራሩ የሚሰጠው ስልጠና የክልሉን ሁለንተናዊ ዕድገት ለማፋጠን የሚያግዝ ነው።
አዳዲስ የፈጠራ ሥራዎች ፈጣን ለውጥ እንዲመጣ ጉልህ ፋይዳ እንዳላቸውም ጨምረው ጠቅሰዋል።
በየደረጃው ያለው አመራር በፈጠራና በፍጥነት የታከለ ለውጥ ፈጣሪ ዜጎችን ለማፍራት እንዲችልና ለዚህም ምቹ ስነ-ምህዳር ለመፍጠር ታስቦ መድረኩ መዘጋጀቱን አስረድተዋል።
ለሦስት ቀናት በሚቆየው ስልጠና በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል እና በስሩ ባሉ 12 ዞኖች የሚገኙ ከፍተኛ አመራሮች በመሳተፍ ላይ ናቸው።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026