የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በባሕር ዳር ከተማ የሰፈነው ሰላም የልማት ስራዎችን ይበልጥ ለማሳለጥ የሚያስችል ምቹ መደላድል ፈጥሯል

Jun 4, 2025

IDOPRESS

ባሕር ዳር፤ ግንቦት 26/2017 (ኢዜአ)፡- በባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር የሰፈነው ሰላም የልማት ስራዎችን ይበልጥ ለማሳለጥ የሚያስችል ምቹ መደላድል መፍጠሩን የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው ተናገሩ።

በከተማው እየተከናውኑ በሚገኙ ዋና ዋና የልማት ኘሮጀክቶች አፈፃፀም ዙሪያ በየደረጃው የሚገኙ አመራር አባላት የተሳተፉበት የምክክር መድረክ ዛሬ በባሕርዳር ተካሄዷል።

ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው በወቅቱ እንደገለጹት፤ ሕዝቡን በማሳተፍ በተከናወነው ሕግ የማስከበር ስራ ሰላምን ማፅናት ተችሏል።


በከተማዋ የሰፈነው ሰላም የቱሪስቶችን ፍሰት ከመጨመር ባለፈ ታላላቅ የልማት ፕሮጀክቶች በፍጥነትና በጥራት ይበልጥ አሳልጦ መስራት የሚያስችል ምቹ መደላድል መፈጠሩን ተናግረዋል።

ለሰላሙ መፅናትና ልማት ስራዎች ሕብረተሰቡ በገንዘቡ፣ በጉልበቱና በእውቀቱ እያደረገ ያለው ያልተቆጠበ ድጋፍ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አንስተው፤ በየደረጃው ያለው አመራርም የሕዝብን የልማት ፍላጎት መሰረት በማድረግ በቁርጠኝነት እየሰራ ነው ብለዋል።

በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአስተዳደሩ ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ሃላፊ አቶ ተሻገር አዳሙ በበኩላቸው፤ በከተማው የሕዝብን ፍላጎት መሰረት ያደረጉ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙ ገልጸዋል።

በዚህም በመጀመሪያውና በሁለተኛው ምዕራፍ 22 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራ ለማከናወን ከታቀደው ውስጥ የመጀመሪያውን ምዕራፍ የ3 ኪሎ ሜትር ማጠናቀቅ መቻሉን ጠቅሰዋል።

የኮሪደር ልማቱ ስማርት ባህርዳርን እውን በማድረግ የሁለተኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማትም መጀመሩን አንስተዋል።

እንዲሁም የ22 ኪሎ ሜትር የኮንክሪት አስፋልት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቁመዋል።

የከተማው ነዋሪ ህንፃዎችን በራሱ ወጪ በማስዋብ፣ ለልማት የሚፈለጉ አካባቢዎችን በፈቃደኝነት በማንሳት ለልማቱ ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር ማሳየቱንም አብራርተዋል።

''የከተማው መሰረተ ልማትና የኮሪደር ልማቱ በዕቅድና አፈፃፀሙ ከሕዝብ ጋር በመወያየትና በመግባባት እየተከናወነ ነው'' ያሉት ደግሞ የከተማ አስተዳደሩ የከንቲባ አደረጃጀት አማካሪ አቶ ጌታቸው ግዛቸው ናቸው።

በከተማው በሚከናወኑ የልማት ስራዎች ከሕብረተሰቡ እስካሁን ከ123 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ መደረጉን ጠቅሰዋል።

መድረኩ ለልማት ስራዎች ሕብረተሰቡ ማድረግ ያለበትን ሁለንተናዊ እገዛ በንቅናቄ አጠናክሮ ማስቀጠል በሚቻልበት ዙሪያ ውይይትና የቀጣይ አቅጣጫ በማስቀመጥ ተጠናቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026