
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 27/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን የማንሰራራት ጉዞ እውን በማድረግ ሂደት ባለሃብቶች ሚናቸውን ሊያጠናክሩ እንደሚገባ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ገለጹ፡፡
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር፣ ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር እና የገቢዎች ሚኒስቴር "ለሁለንተናዊ ብልፅግና የንግዱ ማህበረሰብ ሚና" በሚል መሪ ሀሳብ ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር ምክክር አካሂደዋል፡፡
የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ ሀገረ መንግስት ግንባታ ባለሃብቶች ከፍተኛ ሚና አላቸው፡፡
በኢትዮጵያ ባለፉት ሰባት ዓመታት በተደረገው ሀገራዊ ሪፎርም በኢኮኖሚ፣ በፖለቲካ እና በማህበራዊ መስኮች ተጨባጭ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡

በኢትዮጵያ ከለውጡ በኋላ የተመዘገቡት ስኬቶች ባለሀብቶች መንግስት ለንግድና ኢንቨስትመንት የፈጠረውን ምቹ ከባቢ ወደ ተግባር በመቀየር መሆኑን አንስተዋል፡፡
በኢትዮጵያ ለተመዘገበው ስኬት ባለሃብቶች ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳላቸው በመግለጽ፤ መንግስት ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ጫናዎችን ተቋቁሞ ያመጣው ውጤት መሆኑ መዘንጋት የለበትም ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ ዓለም ዓቀፍ ሁኔታዎችና ሌሎች ፈተናዎችን ወደ እድል እየቀየረች የማንሰራራት ጉዞ ላይ መሆኗን ገልጸዋል፡፡
በኢትዮጵያ ሀገረ መንግስት ግንባታ ባለሃብቶች ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው የገለጹት ሚኒስትሩ፤ ባለሀብቶች ለዘላቂ ሰላምና ልማት መረጋገጥ የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ ማጠናከር አለባቸው ብለዋል፡፡

መንግስት ለሰላም የሚያደርገውን ጥረት መደገፍ እንደሚገባም ነው ሚኒስትሩ ጨምረው የተናገሩት፡፡
የመንግስት ራዕይ ብልጽግናን ማረጋገጥ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ ባለሃብቶች ደግሞ ለስኬታማነቱ ቅርብ ናቸው ሲሉ ገልጸዋል፡፡
በመሆኑም ባለሀብቶች ከኢትዮጵያ ጥንታዊ ስልጣኔ እርሾ በመውሰድና መንግስት የፈጠረውን ምቹ ዕድል በመጠቀም ስራ መፍጠር፣ ምርታማነትን መጨመር እንዳለባቸው አስገንዝበዋል፡፡
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025