የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የኢትዮጵያን የማንሰራራት ጉዞ እውን በማድረግ ሂደት ባለሃብቶች ሚናቸውን ሊያጠናክሩ ይገባል - ሚኒስትር መላኩ አለበል

Jun 5, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 27/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን የማንሰራራት ጉዞ እውን በማድረግ ሂደት ባለሃብቶች ሚናቸውን ሊያጠናክሩ እንደሚገባ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ገለጹ፡፡

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር፣ ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር እና የገቢዎች ሚኒስቴር "ለሁለንተናዊ ብልፅግና የንግዱ ማህበረሰብ ሚና" በሚል መሪ ሀሳብ ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር ምክክር አካሂደዋል፡፡

የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ ሀገረ መንግስት ግንባታ ባለሃብቶች ከፍተኛ ሚና አላቸው፡፡

በኢትዮጵያ ባለፉት ሰባት ዓመታት በተደረገው ሀገራዊ ሪፎርም በኢኮኖሚ፣ በፖለቲካ እና በማህበራዊ መስኮች ተጨባጭ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡


በኢትዮጵያ ከለውጡ በኋላ የተመዘገቡት ስኬቶች ባለሀብቶች መንግስት ለንግድና ኢንቨስትመንት የፈጠረውን ምቹ ከባቢ ወደ ተግባር በመቀየር መሆኑን አንስተዋል፡፡

በኢትዮጵያ ለተመዘገበው ስኬት ባለሃብቶች ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳላቸው በመግለጽ፤ መንግስት ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ጫናዎችን ተቋቁሞ ያመጣው ውጤት መሆኑ መዘንጋት የለበትም ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያ ዓለም ዓቀፍ ሁኔታዎችና ሌሎች ፈተናዎችን ወደ እድል እየቀየረች የማንሰራራት ጉዞ ላይ መሆኗን ገልጸዋል፡፡

በኢትዮጵያ ሀገረ መንግስት ግንባታ ባለሃብቶች ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው የገለጹት ሚኒስትሩ፤ ባለሀብቶች ለዘላቂ ሰላምና ልማት መረጋገጥ የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ ማጠናከር አለባቸው ብለዋል፡፡


መንግስት ለሰላም የሚያደርገውን ጥረት መደገፍ እንደሚገባም ነው ሚኒስትሩ ጨምረው የተናገሩት፡፡

የመንግስት ራዕይ ብልጽግናን ማረጋገጥ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ ባለሃብቶች ደግሞ ለስኬታማነቱ ቅርብ ናቸው ሲሉ ገልጸዋል፡፡

በመሆኑም ባለሀብቶች ከኢትዮጵያ ጥንታዊ ስልጣኔ እርሾ በመውሰድና መንግስት የፈጠረውን ምቹ ዕድል በመጠቀም ስራ መፍጠር፣ ምርታማነትን መጨመር እንዳለባቸው አስገንዝበዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026