
አዲስ አበባ፤ግንቦት 28/2017(ኢዜአ)፦የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙ ከኢትዮጵያ ሁኔታ የተነሳ ከሌሎች የተማረና በኛ ልክ የተሰፋ ሪፎርም ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት ቆይታ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም መነሻ ራስን ከማየት የጀመረ መሆኑን አመልክተዋል።
በኢኮኖሚው ውስጥ ያሉ ችግሮችን ለመፍታት መንግስት ከሀገር ውስጥ እና ከዓለም አቀፍ ባለድርሻ አካላት ጋር መጠነ ሰፊ ውይይቶች ማድረጉን አስታውሰዋል።
በኢኮኖሚ ፈተና ውስጥ ሆነው ወደ ሪፎርም በመሸጋገር ለውጥ ካመጡ ሀገራት ተሞክዎች መወሰዳቸውንም እንዲሁ።
በውይይቶቹ እና ተሞክሮ በመቅሰም የተገኙ ሀሳቦችን መሰረት በማድረግ የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም ወደ ተግባር መግባቱን አንስተዋል።
በሪፎርሙ አማካኝነትም በኢኮኖሚው ላይ የሚታዩ ለውጦች መመዝገባቸውን ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ የገለጹት።
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ሀገር በቀል ነው ሲባል ከሌሎች አንማርም ዝግ ነን ማለት እንዳልሆነ ሊሰመርበት እንደሚገባ አመልክተዋል።
የኢኮኖሚ ሪፎርሙም ለሙሉ ለሙሉ ከውጭ የተቀዳ የሚለው አስተያየት ተገቢ እንዳልሆነም ነው ያነሱት።
ከኢትዮጵያ የውጭ እዳ ጋር በተያያዘ ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት፣ዓለም ባንክ እና ሌሎች አበዳሪዎች ጋር የተደረጉ ድርድሮች የሀገሪቷን ጥቅም እና ፍላጎት ያስጠበቁ መሆናቸውን አመልክተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙ ከኢትዮጵያ ሁኔታ የተነሳ ፣ ከሌሎች የተማረ፣ በኛ ልክ የተሰፋ ሪፎርም መሆኑ ውጤት እንደተገኘበት አንስተዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026