
አዲስ አበባ፤ግንቦት 28/2017(ኢዜአ)፦የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙ ከኢትዮጵያ ሁኔታ የተነሳ ከሌሎች የተማረና በኛ ልክ የተሰፋ ሪፎርም ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት ቆይታ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም መነሻ ራስን ከማየት የጀመረ መሆኑን አመልክተዋል።
በኢኮኖሚው ውስጥ ያሉ ችግሮችን ለመፍታት መንግስት ከሀገር ውስጥ እና ከዓለም አቀፍ ባለድርሻ አካላት ጋር መጠነ ሰፊ ውይይቶች ማድረጉን አስታውሰዋል።
በኢኮኖሚ ፈተና ውስጥ ሆነው ወደ ሪፎርም በመሸጋገር ለውጥ ካመጡ ሀገራት ተሞክዎች መወሰዳቸውንም እንዲሁ።
በውይይቶቹ እና ተሞክሮ በመቅሰም የተገኙ ሀሳቦችን መሰረት በማድረግ የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም ወደ ተግባር መግባቱን አንስተዋል።
በሪፎርሙ አማካኝነትም በኢኮኖሚው ላይ የሚታዩ ለውጦች መመዝገባቸውን ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ የገለጹት።
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ሀገር በቀል ነው ሲባል ከሌሎች አንማርም ዝግ ነን ማለት እንዳልሆነ ሊሰመርበት እንደሚገባ አመልክተዋል።
የኢኮኖሚ ሪፎርሙም ለሙሉ ለሙሉ ከውጭ የተቀዳ የሚለው አስተያየት ተገቢ እንዳልሆነም ነው ያነሱት።
ከኢትዮጵያ የውጭ እዳ ጋር በተያያዘ ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት፣ዓለም ባንክ እና ሌሎች አበዳሪዎች ጋር የተደረጉ ድርድሮች የሀገሪቷን ጥቅም እና ፍላጎት ያስጠበቁ መሆናቸውን አመልክተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙ ከኢትዮጵያ ሁኔታ የተነሳ ፣ ከሌሎች የተማረ፣ በኛ ልክ የተሰፋ ሪፎርም መሆኑ ውጤት እንደተገኘበት አንስተዋል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025