የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የኮሪደር ልማቱ ስነ-ውበትን የገለጠ፣ የተደበቁ ሃብቶችን ጥቅም ላይ ያዋለ እና የሰዎችን ህይወት ያሻሻለ ነው -ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

Jun 9, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ግንቦት 30/2017 (ኢዜአ)፦የኮሪደር ልማቱ ስነ-ውበትን የገለጠ፣የተደበቁ ሃብቶችን ጥቅም ላይ ያዋለ እና የሰዎችን ህይወት ያሻሻለ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አዲስ አበባ ከተማን ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች እየለሙ ያሉ የኮሪደር ልማቶች ከኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታቸው ባሻገር የጤና ጠቀሜታ እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡

ንጽህናው ባልተጠበቀ አካባቢ የሚኖር ማንኛውም ማህበረሰብ የጤናው ሁኔታ አደጋ ውስጥ መውደቁ አይቀርም ነው ያሉት፡፡

በዚህም ምክንያት በአዲስ አበባ እና በሌሎች የክልል ከተሞች የኮሪደር ልማት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

አዲስ አበባ ከተማ ከዚህ በፊት ዝናብ በጣለ ቁጥር አይደለም ለመኖር አልፎ ለመሔድም ከባድ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት በተከናወኑ ሰፊ የልማት ስራዎች ከተማዋ ለጤና፣ ለማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች እጅግ የምትመች አስደማሚ ከተማ እየሆነች መጥታለች ነው ያሉት፡፡

ከመንገድ አኳያም የተሽከርካሪ፣ የእግረኛ እና የብስክሌት መንገዶች ተለይተው በመሰራታቸው አጠቃላይ እንቅስቃሴው የተሳለጠ እንዲሆንና የአደጋዎች ምጣኔ እየቀነሰ እንዲመጣ ማድረጉን ተናግረዋል፡፡

ከዚህ በፊት በሰው ሀገር አይተን የምንቀናባቸውን የልማት ስራዎች አሁን ላይ በሀገራችን ተተግብረው እየታዩ መሆኑን አመልክተው፤ የወንዝ ዳር ልማቶችም ውበትን የገለጡ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

በአጠቃላይ የኮሪደር ልማት ስነ-ውበትን የገለጠ፣ የተደበቁ ሃብቶችን ጥቅም ላይ ያዋለ እና የእያንዳንዱን ሰው ህይወት ያሻሻለ መሆኑን አመልክተዋል፡፡

ከተሜነት በፍጥነት እያደገ እንደሚሔድ ጥናቶችን ዋቢ አድርገው የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የሰው ቁጥር እያደገ በመጣ ቁጥር ደግሞ የከተማ መሰረተ ልማቶችን ማሳደግ ለነገ የማይባል ተግባር መሆኑን አብራርተዋል።

በቀጣይም በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከናወኑ የሚገኙ የኮሪደር ልማትና ሌሎች ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል፡፡

#ኢዜአ #Ethiopia #Ethiopian_News_Agency

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.