አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2017(ኢዜአ)፦ የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት 1 ነጥብ 93 ትሪሊዮን ብር ሆኖ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀረበ።
ምክር ቤቱ ዛሬ ባካሄደው 35ኛ መደበኛ ስብሰባ የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ያቀረቡትን የፌዴራል መንግሥት የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ የበጀት መግለጫ አዳምጧል፡፡
የ2018 በጀት ዓመት የፌደራል መንግሥት ረቂቅ በጀት ተግባራዊ እየተደረገ ያለውን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያና የፊሲካል ፖሊሲን ታሳቢ በማድረግ መዘጋጀቱን ሚኒስትሩ አብራርተዋል፡፡
ለ2018 በጀት ዓመት የተዘጋጀው ረቂቅ በጀት የአስር ዓመቱ መሪ የልማት ዕቅድ አካል የሆነውን የ2016-2018 የልማትና ኢንቨስትመንት እቅድ እና የፕሮግራም በጀት በማጣጣም የተቀመጡ ግቦችና አቅጣጫዎችን ከማስፈጸም አኳያ እና ሊኖር የሚችለውን የሀብት መጠን ከግምት በማስገባት የተዘጋጀ መሆኑን ተናግረዋል።
የተጀመሩ የልማት ስራዎችን ማስቀጠል፣ የመንግስት ብድር ጤናማ እንዲሆን ከአበዳሪዎች ጋር የዕዳ ሽግሽግ ድርድር ማድረግ፣ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የሚያስከትለውን ጫና ለመቀነስ የማህበራዊ ወጪ ድጎማን ማስቀጠል በትኩረት ከሚሰሩት መካከል ጠቅሰዋል።
ከ2017 በጀት አንጻር የ34 ነጥብ 4 በመቶ እድገት እንዳለውም ነው ሚኒስትሩ ያብራሩት፡፡
ወጪው የሚሸፈነው ከ80 በመቶ በላይ ከሀገር ውስጥ ገቢ ሲሆን አዳዲስ የታክስ ምንጮችን ወደ ገቢ ስርዓቱ በማስገባትና የነበሩትን በማጠናከር ገቢን ለመጨመር እንደሚሰራ አብራርተዋል።
በዚህም በ2018 በጀት አመት አጠቃላይ 1 ነጥብ 5 ትሪሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ መታቀዱንም ተናግረዋል።
ባለበጀት መስሪያ ቤቶች የተመደበላቸውን በጀት ለታለመለት አላማ ጥቅም ላይ ማዋል እንዳለባቸውም አሳስበዋል፡፡
በመሆኑም የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት 1 ነጥብ 93 ትሪሊዮን ብር ሆኖ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቧል።
ረቂቅ በጀቱ ለዝርዝር እይታ ለፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ተመርቷል።
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025
ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...
Feb 8, 2025