የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በኢትዮጵያ 23 ተቋማት 124 አገልግሎቶችን በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እየሰጡ ነው - ኮሚሽነር መኩሪያ ሀይሌ(ዶ/ር)

Jun 20, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 12/2017(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ 23 ተቋማት 124 አገልግሎቶችን በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር መኩሪያ ሀይሌ(ዶ/ር) ገለጹ፡፡

ኢትዮጵያ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ማዘመንና የመልካም አስተዳደር ቅሬታን በዘላቂነት መፍታት የሚያስችል ሪፎርም እያከናወነች መሆኑም ኮሚሽነሩ ገለጸዋል።

ኮሚሽነር መኩሪያ ሀይሌ(ዶ/ር) ኢትዮጵያ በትይዩ የምታስተናግዳቸውን 10ኛው የአፍሪካ ሕብረት አባል ሀገራት የመንግሥት አገልግሎት አስተዳደር እና የተመድ የአፍሪካ ቀጣናዊ ፎረም በተመለከተ መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫቸውም ጉባኤዎቹ ከሰኔ 14 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት በአዲስ አበባ አፍሪካ ህብረት መሰብሰቢያ አዳራሽ እንደሚካሄዱ አስታውቀዋል።

የአፍሪካ የመንግሥት አገልግሎትና አስተዳደር ጉባኤ በየሁለት ዓመቱ የሚከናወን አህጉራዊ ኹነት መሆኑ ተመላክቷል።

ጉባኤው የመንግሥት ተቋማት ተለዋዋጭ ሁኔታዎችን ተቋቁመው በየዘመኑ እየተንከባለሉ የመጡ ፈተናዎችን በፍጥነት ለመፍታት እንዲችሉ ያለመ መሆኑን ገልጸዋል።

"የመንግሥት አገልግሎት እና ኢኖቬሽን" በሚል መሪ ሀሳብ በትይዩ የሚከናወነው የተመድ የአፍሪካ ቀጣናዊ ፎረም ፈጠራ በታከለበት መንገድ ሰው ተኮር አገልግሎት መስጠት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።

የ2030 የተመድ 17 ዘላቂ የልማት ግቦችና የአፍሪካ ሕብረት የ2063 አጀንዳ 20 ስትራቴጂያዊ ግቦችን ለማሳካት ጠንካራ ተቋም የመፍጠር ዓላማ እንዳለውም ጠቅሰዋል።

ኢትዮጵያ የተመድ ዘላቂ የልማትና የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ላይ የተቀመጡትን ግቦችን ለማሳካት የመንግሥት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም በመቀየስ የፖሊሲ እና የህግ ማዕቀፍ አዘጋጅታለች ብለዋል።

በተለይም የመንግስትን አገልግሎት ቀልጣፋና ግልጽ ማድረግ የሚያስችል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በመጀመር ውጤታማ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በዚህም በአንድ መሶብ አገልግሎት 23 ተቋማት 124 አገልግሎቶችን እየሰጡ መሆኑን ገልጸው፤ በኢትዮጵያ አዲስ ዓመት ሁሉም ክልሎች ቢያንስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እንዲኖራቸው ይደረጋል ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያ በመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪሮርም እና በአንድ መሶብ አገልግሎት ምክንያት እነዚህን ሁለት አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ኹነቶች በትይዩ እንድታዘጋጅ መመረጧን ተናግረዋል፡፡

በዚህም የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርሙን በሶስት ምዕራፎች በማከናወን በመጀመሪያው ስምንት በሁለተኛው ዘጠኝ እንዲሁም በሶስተኛው ሰባት ተቋማት ላይ ሪፎርሙ ተፈፃሚ ይሆናል ብለዋል።

በሁሉም ምዕራፎች የዝግጅት፣ የተግበራና የማጽናት ምዕራፎች መኖራቸውን ጠቅሰው፤ በመጀመሪያው የሪፎርም ሙከራ ትግበራ ወደ ተግባር ምዕራፍ እየገቡ መሆኑን ገልጸዋል።

የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርሙ የአገልግሎት አሰጣጡን ማዘመን ላይ ትኩረት ማድረጉንም ኮሚሽነሩ ጨምረው ተናግረዋል።

የመንግሥት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም ሥራን ቆጥሮ የሚያስረክብና የሚረከብ ጠንካራ አመራር ለመፍጠር የተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ኢትዮጵያ የመንግስት የአገልግሎት አሰጣጥን ማዘመንና የመልካም አስተዳደር ቅሬታን በዘላቂነት መፍታት የሚያስችል ሪፎርም እያከናወነች መሆኑንም ገለጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026