
ወላይታ ሶዶ፤ ሰኔ 12/2017(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በሚቀጥሉት 90 ቀናት የክልሉን ህዝብ ተጠቃሚነት ይበልጥ የሚያሳድጉ ተግባራት በተቀናጀ መንገድ እንደሚከናወኑ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ተናገሩ።
በመጀመሪያ ዙር የ90 ቀናት ዕቅድ አፈጻጸም ላይ የታዩ ክፍተቶችን በማረም የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ መወሰናቸውንም ከፍተኛ አመራሮቹ ገልጸዋል።
በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የዲላ ክላስተር አስተባባሪ እና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ መሪሁን ፍቅሩ(ዶ/ር)፤ በሚቀጥሉት 90 ቀናት የህዝብን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ተግባራት ይከናወናሉ።
የመኸር እርሻ ስራን ጨምሮ ያሉትን አቅሞች በአግባቡ ለመጠቀም በተቀናጀ መንገድ እንደሚሰራ ጠቅሰው ተግባራቱን በተሻለ ውጤታማ የሚያደርግ ዕቅድ ተዘጋጅቶ እስከታች ድረስ መውረዱን ገልጸዋል።
ባለፉት 90 ቀናትም 844ሺህ ሄክታር ማሳ በበልግ አዝመራ መልማቱንና 119ሺህ የተለያየ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችም ሲተከሉ መቆየታቸውን ተናግረዋል።
የክልሉ መንግስት ረዳት ተጠሪ ንጋቱ ዳንሳ፣ በክልሉ ባለፉት 90 ቀናት ህዝቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።
የሌማት ትሩፋትን በማሳለጥ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በተሰራው ስራ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት የመሸጋገር ሂደትም ጥሩ ደረጃ ላይ ይገኛል ብለዋል።
በቀጣይ 90 ቀናትም የተለጠጠ ዕቅድ በማዘጋጀት ለመፈጸም ከፍተኛ ርብርብ እንደሚደረግ አስረድተዋል።
በክልሉ የወላይታ ዞን የመንግስት ዋና ተጠሪ ዘውዱ ሳሙኤል በበኩላቸው ባለፉት 90 ቀናት የጋራ ትርክት ለማስረጽ የተሰራው ስራ ውጤት አሳይቷል ብለዋል።
በተለይም የአደጋ ስጋትን በራስ አቅም መቋቋም የሚያስችሉ ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን ጠቅሰው ይህን ለማጠናከር እንደሚሰራ ገልጸዋል።
የከተማ ኮሪደር ልማት ደግሞ ከተሞችን ውብና ጽዱ በማድረግ የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ ያለ በመሆኑ ወደ ተለያዩ ከተሞች እያሰፋን እንገኛለን ብለዋል።
የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ(ዶ/ር)፤ ባለፉት 90 ቀናት የህዝቡን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ 31ሺህ ቶን ቡና ለመሰብሰብ ታቅዶ 32ሺህ 500 በላይ ቶን ቡና በመሰብሰብ ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረብ መቻሉን ገልጸዋል።
የህዝቡን ሰላም በማስጠበቅ ዞኑን የፍቅር እና የአንድነት ማዕከል ለማድረግ በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑንም አመልክተዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል 2ኛ ዙር የ90 ቀናት ዕቅድ "ለጥጦ ማቀድ አልቆ መፈጸም'' በሚል መሪ ሃሳብ ከሰኔ 5 እስከ ጳጉሜ 5/ 2017 ዓ. ም ድረስ የሚተገበር መሆኑን ተነግሯል።
ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...
Aug 28, 2026
መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...
Aug 18, 2026
ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...
Aug 10, 2026
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...
Jul 20, 2026