የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የፍጆታ እቃዎች ድጎማን ከማህበረሰቡ ፍላጎትና አቅርቦት ጋር በማጣጣም ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ዜጎች ተደራሽ ማድረግ ይገባል - ቋሚ ኮሚቴው

Jun 20, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 12/2017(ኢዜአ)፦ የፍጆታ እቃዎች ድጎማን ከማህበረሰቡ ፍላጎትና አቅርቦት ጋር በማጣጣም ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ዜጎች ተደራሽ ማድረግ እንደሚገባ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አሳሰበ።

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 38ኛ መደበኛ ስብሰባ የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር የ2017 በጀት ዓመት የ11 ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ተወያይቷል።

የምክር ቤቱ አባላት የጥራጥሬ ምርቶች የወጪ ንግድ አፈጻጸም ዝቅተኛ መሆን፣ የፍጆታ እቃዎች በተለይም ከዘይትና ስኳር ስርጭት ድጎማ ጋር የተያያዙ ችግሮችን አንስተዋል።


የቅዳሜና እሁድ ገበያዎችና የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከላት ተደራሽነት፣ እንዲሁም የጠረፍ ንግድ ስምምነቶች ተግባራዊ ከማድረግ አንጻር የሚታዩ ችግሮችን ለመፍታት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች ሊጠናከሩ እንደሚገባም ገልጸዋል።

እንዲሁም የነዳጅ ማደያዎች በአንዳንድ አካባቢዎች ተደራሽ አለመሆንና ህገ-ወጥ የነዳጅ ስርጭትና ግብይትን አስመልክተው ጥያቄ አንስተዋል፡፡

የንግድ ምዝገባና ፍቃድ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ አመርቂ ውጤቶች ቢመዘገቡም የንግድ ፍቃድን ለመመለስ የሚታየው የቢሮክራሲ ችግር መፈታት ይኖርበታል ብለዋል።

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) እንደተናገሩት አንዳንድ የጥራጥሬ ምርቶች ላይ ዝቅተኛ አፈጻጻም የተገኘው በአለም አቀፍ ዋጋ መቀነስና የአንዳንድ ገዢ ሀገራት ፍላጎት በመቀዛቀዙ ሳቢያ ነው።

የጠረፍ ንግድ ላይ ህገ-ወጥ ንግድ በወጪ ንግድ ላይ ተጽዕኖ እንዳያደርስ ለመቆጣጠር ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚፈልግ በመሆኑ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል።

የነዳጅ ስርጭትና ግብይትን በተመለከተ ተጨማሪ የነዳጅ ማደያዎች የሚያስፈልጉባቸው አካባቢዎችን ለመለየት ጥናት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

የንግድ ምዝገባና ፍቃድ ለመመለስ ከግብር ጋር በተያያዘ የማጣራት ስራዎች ጊዜ የሚፈጁ መሆናቸውን ጠቁመው ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ችግሩን ለመፍታት እንሰራለን ብለዋል።

በመላ ሀገሪቱ በ11 ወራት በተደረገ ክትትል ከ269ሺህ በላይ ድርጅቶች ላይ የህግ መተላለፍ ችግር በመገኘቱ አርምጃ መወሰዱን ጠቅሰዋል።

በድጎማ የሚገቡ የፍጆታ እቃዎች ላይ የሚታየውን የስርጭት ችግር ለመፍታት ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ተጨማሪ ግዢ ለመፈጸም እየሰራን ነው ሲሉም ተናግረዋል።

የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከላት በሁሉም አርብቶ አደሮች አካባቢ ለማስፋፋት እየተሰራ መሆኑንም አስታውቀዋል።

በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አይሻ ያህያ ከ500 ወረዳዎች በላይ የነዳጅ ማደያዎች አለመኖሩን ጠቅሰው፤ ለእነዚህ አካባቢዎች ቅድሚያ በመስጠት በትኩረት ሊሰራ ይገባል ብለዋል።

በየአካባቢዎቹ የነዳጅ ማደያዎችን ገንብተው ወደ ስራ ለመግባት የሚኒስቴሩን ፍቃድ ለሚፈልጉ ባለሀብቶችም ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበዋል።

የፍጆታ እቃዎች ድጎማ በተለይም ዘይትና ስኳር ከማህበረሰቡ ፍላጎትና አቅርቦት ጋር በማጣጣም ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ዜጎች ተደራሽ ማድረግ እንደሚገባም አሳስበዋል።

ደረጃቸውን ያልጠበቁ ምርቶችን የሚያመርቱና ወደ ሀገር ውስጥ የሚያስገቡ ተቋማት ላይ ጠንካራ ህጋዊ እርምጃ መወሰድ አለበትም ነው ያሉት።

በወጪ ንግድ የተገኘው ገቢ ትልቅ ሰኬት መሆኑን ገልጸው፤ ሀገሪቱ ካላት እምቅ አቅም አንጻር ገቢው እንዲጨምር የሚከናወኑ ስራዎች ሊጠናከሩ እንደሚገባም አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026