
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2017(ኢዜአ)፦ በህገ-ወጥ ነዳጅ ማደያዎች ላይ የሚወሰደው ህጋዊ እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገለጹ፡፡
ሚኒስትሩ ከነዳጅ ግብይት ጋር ተያይዞ በነዳጅ ማደያዎች የተስተዋለውን ሰልፍ በተመለከተ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም መንግስት በማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የነዳጅ ዋጋን ከአለም ዋጋ ጋር የማጣጣም ስራ መስራቱን ገልጸዋል፡፡
በዚህም በየወሩ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ እንደማይኖር ጠቁመው፤ የነዳጅ ዋጋ በአለም አቀፍ የነዳጅ መሸጫ ዋጋ ይወሰናል ብለዋል፡፡
አንዳንድ ነዳጅ ማደያዎች የዋጋ ማሻሻያ ይኖራል ብለው በማሰብ ሰው ሰራሽ የነዳጅ እጥረት እንዲፈጠር አድርገዋል ነው ያሉት ሚኒስትሩ በመግለጫቸው።
በአዲስ አበባ ምንም አይነት የነዳጅ ዋጋ ጭማሪም ሆነ የአቅርቦት እጥረት አለመኖሩን በክትትል ማረጋገጥ መቻሉን ገልጸዋል፡፡
በተደረገው ክትትል አዲስ አበባ ውስጥ 2 ነጥብ 3 ሚሊዮን ሊትር ነጭ ናፍጣ እና 3 ሚሊዮን ሊትር ቤንዚን መኖሩን ማረጋገጥ መቻሉን አመላክተዋል፡፡
በድምሩ 5 ነጥብ 3 ሚሊየን ሊትር ነዳጅ እያለ ነው በህገ ወጦች የነዳጅ እጥረት እንዳለ ለማስመሰል ሙከራ የተደረገው ብለዋል፡፡
ይህ በአቋራጭ ለመክበርና የራስ ያልሆነን ገንዘብ ለማጋበስ የሚደረግ ጥረት መሆኑን አመልክተው በዚህ ህገ-ወጥ ስራ ላይ ተሰማርተው የተገኙ ሁለት የነዳጅ ማደያዎች ሙሉ ለሙሉ ከግብይት ስርዓቱ እንዲወጡ መደረጉን ገልጸዋል፡፡
በህገ-ወጥ ነዳጅ ማደያዎች ላይ የሚወሰደው መሰል ህጋዊ እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ነው ሚኒስትሩ ያስታወቁት፡፡
መንግስት ከአራት ቢሊዮን ዶላር በላይ እያወጣ የነዳጅ ምርት እያቀረበ እንደሚገኝ አመላክተው የምርት እጥረት ሳይኖር እንዳለ የሚያስመስሉ ህገ-ወጦች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡም አሳስበዋል፡፡
በንግድ አዋጁ መሰረት ምርቶችን የመደበቅ ወንጀል ከ300 ሺህ እስከ 500 ሺህ ብር የሚደርስ የገንዘብ ቅጣት እና የማደያ ባለቤቱን ከ2 እስከ 5 ዓመት እስራት የሚደርስ የእስር ቅጣት እንደሚያስቀጣ ጠቁመዋል፡፡
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025