
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2017(ኢዜአ)፦ በህገ-ወጥ ነዳጅ ማደያዎች ላይ የሚወሰደው ህጋዊ እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገለጹ፡፡
ሚኒስትሩ ከነዳጅ ግብይት ጋር ተያይዞ በነዳጅ ማደያዎች የተስተዋለውን ሰልፍ በተመለከተ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም መንግስት በማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የነዳጅ ዋጋን ከአለም ዋጋ ጋር የማጣጣም ስራ መስራቱን ገልጸዋል፡፡
በዚህም በየወሩ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ እንደማይኖር ጠቁመው፤ የነዳጅ ዋጋ በአለም አቀፍ የነዳጅ መሸጫ ዋጋ ይወሰናል ብለዋል፡፡
አንዳንድ ነዳጅ ማደያዎች የዋጋ ማሻሻያ ይኖራል ብለው በማሰብ ሰው ሰራሽ የነዳጅ እጥረት እንዲፈጠር አድርገዋል ነው ያሉት ሚኒስትሩ በመግለጫቸው።
በአዲስ አበባ ምንም አይነት የነዳጅ ዋጋ ጭማሪም ሆነ የአቅርቦት እጥረት አለመኖሩን በክትትል ማረጋገጥ መቻሉን ገልጸዋል፡፡
በተደረገው ክትትል አዲስ አበባ ውስጥ 2 ነጥብ 3 ሚሊዮን ሊትር ነጭ ናፍጣ እና 3 ሚሊዮን ሊትር ቤንዚን መኖሩን ማረጋገጥ መቻሉን አመላክተዋል፡፡
በድምሩ 5 ነጥብ 3 ሚሊየን ሊትር ነዳጅ እያለ ነው በህገ ወጦች የነዳጅ እጥረት እንዳለ ለማስመሰል ሙከራ የተደረገው ብለዋል፡፡
ይህ በአቋራጭ ለመክበርና የራስ ያልሆነን ገንዘብ ለማጋበስ የሚደረግ ጥረት መሆኑን አመልክተው በዚህ ህገ-ወጥ ስራ ላይ ተሰማርተው የተገኙ ሁለት የነዳጅ ማደያዎች ሙሉ ለሙሉ ከግብይት ስርዓቱ እንዲወጡ መደረጉን ገልጸዋል፡፡
በህገ-ወጥ ነዳጅ ማደያዎች ላይ የሚወሰደው መሰል ህጋዊ እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ነው ሚኒስትሩ ያስታወቁት፡፡
መንግስት ከአራት ቢሊዮን ዶላር በላይ እያወጣ የነዳጅ ምርት እያቀረበ እንደሚገኝ አመላክተው የምርት እጥረት ሳይኖር እንዳለ የሚያስመስሉ ህገ-ወጦች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡም አሳስበዋል፡፡
በንግድ አዋጁ መሰረት ምርቶችን የመደበቅ ወንጀል ከ300 ሺህ እስከ 500 ሺህ ብር የሚደርስ የገንዘብ ቅጣት እና የማደያ ባለቤቱን ከ2 እስከ 5 ዓመት እስራት የሚደርስ የእስር ቅጣት እንደሚያስቀጣ ጠቁመዋል፡፡
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026