የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በሲዳማ ክልል ከ80 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ ይለማል

Sep 30, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

‎ሀዋሳ፤ መስከረም 19/2018 (ኢዜአ) :- በሲዳማ ክልል በዘንድሮው በጋ ከ80 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ እንደሚለማ የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ገለፀ ።

‎በሲዳማ ክልል የ2018 የምርት ዘመን የበጋ መስኖ ልማት የንቅናቄ መድረክ ተካሄዷል።

‎የቢሮው ኃላፊ አቶ መምሩ ሞኬ እንደገለፁት በክልሉ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና ገበያን ለማረጋጋት ለመስኖ ልማት ሥራ ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል፡፡


ይህም ባለፉት ዓመታት በመስኖ የሚለማ መሬት ሽፋንን በማሳደግ የምርት መጠን እንዲጨምር መደረጉን ገልፀዋል፡፡

ለአብነትም ባለፈው ዓመት በበጋ መስኖ 73 ሺህ ሄክታር መሬት ማልማት እንደተቻለ ጠቅሰው ይህንንም በዘንድሮው በጋ ከ80 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ለማሳደግ መታቀዱን ጠቁመዋል ።

አርሶ አደሩ የመስኖ አውታሮችን ለማልማት ኩሬዎችን፣ አነስተኛ ጉድጓዶችን፣ ጅረቶችንና ወንዞችን ጨምሮ ሁሉንም የውሃ አማራጭ ተጠቅሞ በማልማት ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ በዓመት ሁለትና ሶስት ጊዜ ማምረት እንዲችል እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል ፡፡

የክልሉ መንግስት ዝናብ አጠር በሆኑ አካባቢዎች ላይ ከፍተኛ በጀት በመመደብና ጥልቅ የውሃ ጉድጓዶችን በመቆፈር ከዚህ ቀደም በመስኖ ልማት የማይታወቁ አካባቢዎች ጭምር ዓመቱን ሙሉ እንዲያመርቱ ማድረግ መቻሉን ገልፀዋል፡፡


የቢሮው ምክትልና የእርሻ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ባንጉ በቀለ በበጋ የመስኖ ልማት ከ80 ሺህ 55 ሄክታር በላይ መሬት በማልማት ከ18 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት መታቀዱን አስረድተዋል፡፡

ከመስኖ ልማቱም ከ24 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆነው መሬት በኩታ ገጠም የሚለማ መሆኑን ጠቁመው በዚህ የልማት ሥራም ከ350 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ እንደሚሆኑም ጠቅሰዋል፡፡

ምርጥ ዘር፣ የአፈር ማዳበሪያ እንዲሁም ሌሎች ግብዓቶች በበቂ ሁኔታ ለአርሶ አደሩ እንዲደርሱ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መሰራታቸውን ተናግረዋል፡፡

በንቅናቄ መድረኩ ላይም የክልሉ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026