🔇Unmute
ማያ ፤ መስከረም 30/2018 (ኢዜአ)፡-በኦሮሚያ ክልል የማያ ከተማ መስተዳደር ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ በመሰብሰብ የህዝብን የልማት ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ።
የከተማው መስተዳድር ገቢዎች ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አብዲ ዩያ ለኢዜአ እንደገለጹት ፤ በከተማ መስተዳድሩ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ ለመሰብሰብ በሚከናወነው ስራ በየዓመቱ የሚሰበሰበው ገቢ እየጨመረ ነው።
በዚሁ ልክ በሶስቱም ክፍለ ከተሞች ለህዝብ የልማት ጥያቄዎች ምላሽ እየተሰጠ ይገኛል ብለዋል።
በዘንድሮ በጀት ዓመትም ቀጥታና ቀጥታ ካልሆኑ ታክሶች እንዲሁም ከማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ከ2 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ ለመሰብሰብ ታቅዶ በመጀመሪያዎቹ ሶስት ወራት ከ658 ሚሊዮን ብር በላይ መሰብሰቡን ጠቅሰዋል።
የገቢ አሰባሰቡ እቅዱን ሙሉ ለሙሉ ማሳካት በሚቻል መልኩ መከናወኑን የጠቀሱት ሃላፊው ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ደግሞ በ271 ሚሊየን ብር ብልጫ ማሳየቱን አመላክተዋል።
ለገቢው መጨመር የተቀመጡትን የገቢ ርዕሶች በአግባቡ ለመተግበር የተካሄደው የተቀናጀ ጥረትና የግብር ከፋዩ ህብረተሰብ ግብርን የመክፈል ግንዛቤ እያደገ መምጣት ተጠቃሽ መሆናቸውን አቶ አብዲ አስረድተዋል።
የክልሉ መንግስት ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት በራስ ገቢ ወጪን ለመሸፈን የተጀመረውን ጥረት ለማሳካት ጥረቱ ተጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል።
የግብር ገቢው በየዓመቱ መጨመር የህዝብ የልማት ተጠቃሚነት እንዲጎለብት እያስቻለ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በከተማ መስተዳድሩ የሚሰበሰበው ገቢ ላይ ተጽዕኖ የሚያስከትለውን የኮንትሮባንድ ንግድ በመከላከል ረገድ የሚከናወነው የተቀናጀ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
ህገ ወጥ ነጋዴዎችን ወደ ህጋዊ መስመር የማስገባትና ደረሰኝ በማይቆርጡ የንግድ ድርጅቶች ላይም የሚከናወነው የቁጥጥርና ክትትል ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።
ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...
Aug 28, 2026
መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...
Aug 18, 2026
ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...
Aug 10, 2026
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...
Jul 20, 2026