🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያ በየዓመቱ የሚከበሩ የአደባባይ በዓላት የሀገር ውስጥ ቱሪዝምን በማስፋፋት ለዘርፉ እድገት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከቱ እንደሚገኙ ቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ።
የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ እንደገና አበበ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንዳሉት፤ መንግስት ቱሪዝምን እንደ ትልቅ የኢኮኖሚ መስክ በመውሰድ ዘርፉን የሚያነቃቁ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል።
በኢትዮጵያ የሚገኙ የተፈጥሮ ሀብቶችን፣ ታሪካዊ ቅርሶችን እንዲሁም የማይዳሰሱ ትውፊቶችን በአግባቡ ለመጠቀምና በዘርፉ የሚታዩ ችግሮችን ለመፍታት በከፍተኛ ደረጃ መሰራቱ አንስተዋል።
በመዲናዋ ያሉ የቱሪስት መዳረሻ ቦታዎችን ማስፋት መቻሉ የሀገር ውስጥና የውጭ ጎብኚዎችን ቁጥር በመጨመር ከዘርፉ የሚገኘውን ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ እንዲያድግ ማስቻሉንም ተናግረዋል፡፡
በመላው ሀገሪቱ የሚከበሩ የአደባባይ በዓላት የቱሪዝም ዘርፉን በማነቃቃት የሀገር ገፅታ በመገንባት ረገድ አቅም እየፈጠሩ እንደሚገኙ ጠቁመዋል።
በተለይም በዩኔስኮ የተመዘገቡ ቅርሶች ዓለም አቀፍ እውቅና ያላቸው መሆናቸውን ጠቁመው፤ ለሀገር ውስጥ የቱሪዝም እድገት ፋይዳቸው ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል።
ቅርሶቹ ከውጪ ጎብኚዎች ከሚገኘው ገቢ በላይ በዩኔስኮ በኩል ለጥናትና ምርምር የሚመጡት ሃብቶች በርካታ መሆናቸውንም ጠቁመዋል።
እንዲሁም የኢትዮጵያ ትርክቶችን ለዓለም በማስተዋወቅ አትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ በአፍሪካ ያላትን ቦታ በማጉላት የሚያበረክቱት አስተዋፅኦ ከፍተኛ ነው ብለዋል።
የአደባባይ በዓላቱ ሲከበሩ የሀገር ባህል ልብስ በስፋት የሚፈለግበት ወቅት መሆኑን ጠቅሰው፤ የስራ እድል ከመፍጠር አኳያም ትልቅ አስተዋፅኦ እያበረከቱ እንደሚገኙ ሚኒስትር ዴኤታው ገልፀዋል።
በቱሪዝም መዳረሻዎች አስፈላጊው መሰረት ልማት እንዲሟላ መደረጉ ለጎብኚዎች እርካታ ከመፍጠር ባለፈ ቆይታቸውን እንዲያራዝሙ እያደረገ እንደሚገኝ ነው የገለጹት፡፡
በተለይም በመዲናዋ የተሰሩ የቱሪስት መስህብ ስፍራዎች፣ መሰረተ ልማቶች እንዲሁም የኮሪደር ልማት ስራዎች ከፍተኛ የሆነ የኢኮኖሚ ጠቀሜታ እያስገኙ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
የኮሪደር ልማቱ የበዓላቱ ልዩ ድምቀት የሰጠ እና የበዓሉ ታዳሚዎች ያለ ምንም መገፋፋት በነፃነት እንዲያከብሩ ማስቻሉንም ጠቁመዋል።
በዚህም የኮሪደር ልማት ለቱሪዝም እድገት የመጣ ሲሳይ ነው ብለን መግለፅ እንችላለን ብለዋል።
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025
ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...
Feb 8, 2025