🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 15/2018(ኢዜአ)፦ ከቅዳሜና እሁድ የገበያ አማራጮች መሰረታዊ የፍጆታ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እያገኙ መሆኑን አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ሸማቾች ተናገሩ።
የኑሮ ውድነትን ለመከላከልና ገበያን ለማረጋጋት የቅዳሜና እሁድ የገበያ አማራጮች ጉልህ ሚና እየተጫወቱ ነው።
በእነዚህ ገበያዎች የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች ቀጥታ ከአምራቹ ወደ ሸማቹ እየቀረቡ ይገኛሉ።
ይህም ሸማቹ የሚፈልጋቸውን ምርቶች በቀላሉ እንዲያገኝ ዕድል ፈጥሯል።
ኢዜአ በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ የቅዳሜና እሁድ የገበያ ስፍራዎች ላይ ባደረገው ቅኝትም ይህን ማረጋገጥ ችሏል።
በቅዳሜ ገበያ ግብይት ሲፈጽሙ ካገኘናቸው መካከል ማርታ ዳምጠው አንዷ ናቸው።

እርሳቸው እንደሚሉት፤ በቅዳሜና እሁድ ገበያ የሚቀርቡ መሰረታዊ የፍጆታ እቃዎች የሸማቹን ፍላጎትና የመግዛት አቅም ያማከሉ ናቸው።
ሌላው አስተያየት ሰጪ ታምሩ አያና የቅዳሜና እሁድ ገበያ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኙ ዕድል የፈጠረላቸው መሆኑን ገልጸው፤ ገበያው በሁሉም አካባቢዎች ሊስፋፋ እንደሚገባ ጠቁመዋል።

የቅዳሜና እሁድ ገበያ መሰረታዊ ሸቀጦችን በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኙ ያስቻላቸው መሆኑን የተናገሩት ደግሞ ሌላው አስተያየት ሰጪ ሀብታሙ አጎናፍር ናቸው።

ነጋዴዎች በበኩላቸው፤ ጥራት ያላችው መሰረታዊ ምርቶችን በብዛትና በበቂ መጠን እንዲሁም በተመጣጣኝ ዋጋ ለሸማቹ እያቀረቡ መሆኑን ገልጸዋል።
ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...
Aug 28, 2026
መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...
Aug 18, 2026
ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...
Aug 10, 2026
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...
Jul 20, 2026