🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፡-በኢትዮጵያ የሚከናወኑ ሜጋ ፕሮጀክቶች በታለመላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ መንግስት በልዩ ክትትልና ትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እየተካሔደ ይገኛል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከምክር ቤት አባላት የግንባታ ሒደት ላይ ያሉና መሰረት የተቀመጠላቸው ሜጋ ፕሮጀክቶችን በሚመለከት ለተነሳላቸው ጥያቄ በሰጡት ማብራሪያ የሀገርን ኢኮኖሚ ወደ ተሻለ ደረጃ የሚያሸጋግሩ ፕሮጀክቶች እውን ሆነዋል ብለዋል።
በኢትዮጵያ በተካሔደው ሀገራዊ ሪፎርም የማዕድን ሀብትን አሟጦ መጠቀም የሚያስችል የአሰራር ስርዓት ተግባራዊ መደረጉን አንስተው የጋዝ፣ የነዳጅና ሌሎች ማዕድናትን ወደ ጥቅም የሚቀይሩ ሜጋ ፕሮጀክቶች መጀመራቸውን ተናግረዋል።
የአፈር ማዳበሪያን በሀገር ውስጥ ማምረትና መጠቀም የሚያስችል ግዙፍ ፋብሪካ ከዳንጎቴ ጋር በመተባበር ወደ ግንባታ መግባቱን ገልጸው፥ ይህም የኢትዮጵያን አርሶ አደሮች የብዙ ዘመናት ችግር የሚፈታ ነው ብለዋል።
በዓመት 100 ሚሊዮን መንገደኞችን ማስተናገድ የሚችለው ግዙፉ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ የዲዛይን ስራ ሙሉ ለሙሉ መጠናቀቁንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው ጠቁመዋል።
በአጠቃላይ የአውሮፕላን ማረፊያ ግንባታው ኢትዮጵያን የአፍሪካ አቪየሽን ማዕከል የሚያደርጋት መሆኑን ተናግረው፥ ለ ሜጋ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ መጠናቀቅ መንግሥት በልዩ ትኩረት ይሰራል ነው ያሉት።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026