የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

መንግሥት ሜጋ ፕሮጀክቶች በታለመላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ በልዩ ክትትልና ትኩረት እየሰራ ይገኛል

Oct 29, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፡-በኢትዮጵያ የሚከናወኑ ሜጋ ፕሮጀክቶች በታለመላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ መንግስት በልዩ ክትትልና ትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።

6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እየተካሔደ ይገኛል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከምክር ቤት አባላት የግንባታ ሒደት ላይ ያሉና መሰረት የተቀመጠላቸው ሜጋ ፕሮጀክቶችን በሚመለከት ለተነሳላቸው ጥያቄ በሰጡት ማብራሪያ የሀገርን ኢኮኖሚ ወደ ተሻለ ደረጃ የሚያሸጋግሩ ፕሮጀክቶች እውን ሆነዋል ብለዋል።

በኢትዮጵያ በተካሔደው ሀገራዊ ሪፎርም የማዕድን ሀብትን አሟጦ መጠቀም የሚያስችል የአሰራር ስርዓት ተግባራዊ መደረጉን አንስተው የጋዝ፣ የነዳጅና ሌሎች ማዕድናትን ወደ ጥቅም የሚቀይሩ ሜጋ ፕሮጀክቶች መጀመራቸውን ተናግረዋል።

የአፈር ማዳበሪያን በሀገር ውስጥ ማምረትና መጠቀም የሚያስችል ግዙፍ ፋብሪካ ከዳንጎቴ ጋር በመተባበር ወደ ግንባታ መግባቱን ገልጸው፥ ይህም የኢትዮጵያን አርሶ አደሮች የብዙ ዘመናት ችግር የሚፈታ ነው ብለዋል።

በዓመት 100 ሚሊዮን መንገደኞችን ማስተናገድ የሚችለው ግዙፉ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ የዲዛይን ስራ ሙሉ ለሙሉ መጠናቀቁንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው ጠቁመዋል።

በአጠቃላይ የአውሮፕላን ማረፊያ ግንባታው ኢትዮጵያን የአፍሪካ አቪየሽን ማዕከል የሚያደርጋት መሆኑን ተናግረው፥ ለ ሜጋ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ መጠናቀቅ መንግሥት በልዩ ትኩረት ይሰራል ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026