🔇Unmute
ሮቤ ፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ)፡-በባሌ ዞን በግብይት ውስጥ ህገወጥ ተግባር የፈጸሙ 1 ሺህ 704 ነጋዴዎች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱን የዞኑ ንግድ ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።
የጽሕፈት ቤቱ ሃላፊ ሙሲና አብደላ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ በዞኑ ከመንግስት ሰራተኞች ደመወዝ ማሻሻያ ጋር ተያይዞ በምርቶች ላይ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ የሚያደርጉ አካላትን ለይቶ ለመቆጣጠር ግብረ ሃይል ተቋቁሞ ጥብቅ ክትትልና ቁጥጥር እየተደረገ ነው።

በዞኑ አስር ወረዳዎች የተቋቋመው ግብረ ሃይል 9 ሺህ 900 በሚጠጉ ነጋዴዎች ላይ ባደረገው የቁጥጥርና ክትትል ስራ 1 ሺህ 705 የሚሆኑ ነጋዴዎች ሕግ ተላልፈው መገኘታቸውን አመልክተዋል።

በግብረ ሀይሉ ከተለዩት ሕገ ወጥ ተግባራት መካከል የንግዱ ማሀበረሰብ በሚያቀርበው ምርት ላይ የዋጋ ዝርዝር አለመለጠፍ፣ ምክንያታዊ ያልሆነ የተጋነነ የዋጋ ጭማሪ ማድረግ፣ ግልፅ መረጃ ለሸማቹ አለመስጠት እንደሚገኙበት አንስተዋል።
በዚህም ሕገ ወጥ ድርጊቶችን ፈጽመው በተገኙ 1 ሺህ 704 ነጋዴዎች በሚያንቀሳቅሱት የንግድ ድርጅቶች ላይ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ፣የማሸግና ሌሎች አስተዳደራዊ እርምጃዎች መወሰዱን አስታውቀዋል።

ከሕገ ወጥ ተግባራቸው በማይመለሱ ነጋዴዎች ላይ የንግድ ፈቃድ እገዳና እስከ መሰረዝ የሚደርስ እርምጃ እንደሚወሰድ ገልጸዋል።
በየደረጃው የሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎችም ምርትን በመደበቅና ያለአግባብ ዋጋ በመጨመር ድርጊት ላይ የተሰማሩ የንግድ ድርጅቶችን በመጠቆም የተለመደ ትብብራቸውን እንዲያደርጉ አሳስበዋል።
በሮቤ ከተማ ነዋሪ ወጣት ሲፈን ግርማ በሰጠችው አስተያየት፤ ተገቢ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ እንዳይከሰት በመንግስት እየተሰራ ያለው ተግባር ገበያው እንዲረጋጋ በማድረጉ ይሄው ተግባር እንዲቀጥል ጠይቃለች።

ምክንያታዊ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ ነጋዴዎች ላይ የተጀመረው የቁጥጥር ስራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የገለጹት ደግሞ ወይዘሮ መሰረት አድማሱ ናቸው።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025