የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በባሌ ዞን በግብይት ውስጥ ህገወጥ ተግባር የፈጸሙ 1 ሺህ 704 ነጋዴዎች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ ተወሰደ

Oct 31, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ሮቤ ፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ)፡-በባሌ ዞን በግብይት ውስጥ ህገወጥ ተግባር የፈጸሙ 1 ሺህ 704 ነጋዴዎች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱን የዞኑ ንግድ ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።

የጽሕፈት ቤቱ ሃላፊ ሙሲና አብደላ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ በዞኑ ከመንግስት ሰራተኞች ደመወዝ ማሻሻያ ጋር ተያይዞ በምርቶች ላይ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ የሚያደርጉ አካላትን ለይቶ ለመቆጣጠር ግብረ ሃይል ተቋቁሞ ጥብቅ ክትትልና ቁጥጥር እየተደረገ ነው።


በዞኑ አስር ወረዳዎች የተቋቋመው ግብረ ሃይል 9 ሺህ 900 በሚጠጉ ነጋዴዎች ላይ ባደረገው የቁጥጥርና ክትትል ስራ 1 ሺህ 705 የሚሆኑ ነጋዴዎች ሕግ ተላልፈው መገኘታቸውን አመልክተዋል።


በግብረ ሀይሉ ከተለዩት ሕገ ወጥ ተግባራት መካከል የንግዱ ማሀበረሰብ በሚያቀርበው ምርት ላይ የዋጋ ዝርዝር አለመለጠፍ፣ ምክንያታዊ ያልሆነ የተጋነነ የዋጋ ጭማሪ ማድረግ፣ ግልፅ መረጃ ለሸማቹ አለመስጠት እንደሚገኙበት አንስተዋል።

በዚህም ሕገ ወጥ ድርጊቶችን ፈጽመው በተገኙ 1 ሺህ 704 ነጋዴዎች በሚያንቀሳቅሱት የንግድ ድርጅቶች ላይ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ፣የማሸግና ሌሎች አስተዳደራዊ እርምጃዎች መወሰዱን አስታውቀዋል።


ከሕገ ወጥ ተግባራቸው በማይመለሱ ነጋዴዎች ላይ የንግድ ፈቃድ እገዳና እስከ መሰረዝ የሚደርስ እርምጃ እንደሚወሰድ ገልጸዋል።

በየደረጃው የሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎችም ምርትን በመደበቅና ያለአግባብ ዋጋ በመጨመር ድርጊት ላይ የተሰማሩ የንግድ ድርጅቶችን በመጠቆም የተለመደ ትብብራቸውን እንዲያደርጉ አሳስበዋል።

በሮቤ ከተማ ነዋሪ ወጣት ሲፈን ግርማ በሰጠችው አስተያየት፤ ተገቢ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ እንዳይከሰት በመንግስት እየተሰራ ያለው ተግባር ገበያው እንዲረጋጋ በማድረጉ ይሄው ተግባር እንዲቀጥል ጠይቃለች።


ምክንያታዊ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ ነጋዴዎች ላይ የተጀመረው የቁጥጥር ስራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የገለጹት ደግሞ ወይዘሮ መሰረት አድማሱ ናቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026