🔇Unmute
ሐረር፤ህዳር 2/2018 (ኢዜአ)፦የሐረሪ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ።
የሐረሪ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ እና የኢፌዴሪ ፐብሊክ ሰርቪስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አልማዝ መሰለ በተገኙበት ነው ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት የሆነው።

በከተማው የተገነባው ማዕከሉ በመጀመሪያ ምዕራፍ በሰባት ተቋማት 22 አገልግሎቶችን አቀናጅቶ የሚሰጥ መሆኑም ታውቋል።
የሐረሪ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እነዚህን አገልግሎቶች በተቀናጀ መንገድ መስጠት በሚያስችል መልኩ በሰው ሃይልና በቴክኖሎጂ ተደራጅቶ ወደ ስራ መግባቱ ነው የተገለጸው።
በመርሃ ግብሩ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪና የኢፌዴሪ ፐብሊክ ሰርቪስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አልማዝ መሰለን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...
Aug 28, 2026
መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...
Aug 18, 2026
ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...
Aug 10, 2026
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...
Jul 20, 2026