🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ህዳር 2/2018(ኢዜአ)፦ በደብረ ብርሃን ከተማ ከ 150 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ስራ መግባታቸውን የከተማዋ ከንቲባ በድሉ ውብሸት ገለጹ፡፡
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ደብረ ብርሃን ከተማ የተገነባውን ብራውን ፉድ የበቆሎ፣ ብቅልና አልሚ ምግብ ማምረቻ ፋብሪካ መርቀዋል።
በሥነ ሥርዓቱ ላይ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ፣ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማህበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ሙዓዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረትን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የፌዴራልና የክልል የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
የደብረ ብርሃን ከተማ ከንቲባ በድሉ ውብሸት በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የለውጡ መንግስት ለልማት በሰጠው ትኩረት በኢንዱስትሪና ከተማ ልማት እመርታዊ ስኬት ተመዝግቧል፡፡
የደብረብርሃን ከተማ በኢትዮጵያ የተመዘገበው ለውጥ ተቋዳሽ መሆኗን በማንሳት፤ ባለፉት ዓመታት ከ150 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ስራ መግባታቸውን ገልጸዋል፡፡
ወደ ስራ የገቡ አምራች ኢንዱስትሪዎቹ ከ30 ሺህ በላይ ለሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠራቸውን ገልጸው፤ ወደ ሙሉ ማምረት ሲሸጋገሩ አሃዙ ወደ 150 ሺህ ከፍ ይላል ብለዋል፡፡
ከተማዋ ለአዲስ አበባ ያላት ቅርበት፣ ኢንዱስትሪን እንደ ዐይኑ ብሌን የሚመለከት ሰላም ወዳድ ማህበረሰብ መኖሩና የአገልግሎት አሰጣጥ መሻሻሉ ለኢንዱስትሪው መስፋፋት ገንቢ ሚና ተጫውቷል ብለዋል፡፡
ዘመናዊ የቆሻሻ ማስወገጃ፣ የኮሪደር ልማት እና ሌሎች የመሠረተ ልማት ግንባታዎች መከናወናቸውን በመጥቀስ፤ የመንግስትን አገልግሎት ለማሳለጥ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሥርዓት መዘርጋቱን ገልጸዋል፡፡
ባለፉት ሦስት ዓመታት ከ30 ሺህ በላይ ዜጎች የመኖሪያ ቦታ ማግኘታቸውን ገልጸው፤ በ2018 በጀት ዓመት 10 ሺህ ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ ዝግጅት ተደርጓል ብለዋል፡፡
የብራውን ፉድ ፋብሪካ የበቆሎ ምርትን በመጠቀም በቫይታሚን የበለጸጉ የምግብ ምርቶች እና የእንስሳት መኖ በማምረት የግብርና ምርታማነትን ለማሻሻል እንደሚያግዝ ገልጸዋል፡፡
የብራውን ፉድ ፋብሪካ ባለቤት ብሩክ ወርቁ ፋብሪካው የበቆሎ ምርትን በግብዓትነት የሚጠቀም መሆኑን በመግለጽ፤ ገቢ ምርትን ማስቀረት ያስችላል ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የበቆሎ ምርትን በመጠቀም በቫይታሚን የበለጸገ አልሚ ምግቦችን ዓለም አቀፍ ደረጃውን በጠበቀ ጥራትና ብዛት ለገበያ ለማቅረብ እንደሚያስችላቸውም ገልጸዋል፡፡
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025