🔇Unmute
ባሕር ዳር ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦የጣናነሽ ቁጥር - ሁለት ጀልባ ሥራ መጀመር በጣና ሐይቅ ሲሰጥ የቆየውን የትራንስፖርት አገልግሎት ይበልጥ በማዘመን የቱሪዝም ዘርፉን እያነቃቃ መምጣቱን በባሕር ዳር ከተማ አስጎብኚዎች ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባለፈው ሳምንት በባሕር ዳር ከተማ ተገኝተው ጣናነሽ ቁጥር-2 ጀልባን ሥራ በይፋ ማስጀመራቸው የሚታወስ ነው።
የጀልባዋን ሥራ መጀመር በማስመልከት ኢዜአ ያነጋገራቸው የባሕር ዳር ከተማ አስጎብኚዎች እንዳሉት፤ የጀልባዋ ወደሥራ መግባት በጣና ሐይቅ ላይ የነበረን ዘመኑን የማይመጥን የትራንስፖርት አገልግሎት ቀይሮታል።
አገልግሎቱን በማዘመን ዘርፉን እያነቃቃው መምጣቱንም ነው የተናገሩት።

ከአስጎብኚዎቹ መካከል አቶ አበበ ያረጋል፤ የጀልባዋን ሥራ መጀመር በተለይ በቱሪዝም ዘርፍ የተሰማራው ማህበረሰብ በጉጉት ሲጠብቀው እንደቆየ ተናግረዋል።
ለቱሪስቶች በጣና ሐይቅ ላይ የሚገኙ ታሪካዊና ባሕላዊ የመስህብ ሃብቶችን ለመጎብኘት ትልቅ ዕድል ይዞ መምጣቱንም ተናግረዋል።
ከዚህ ቀደም በጣና ሐይቅ ዘመኑን በማይዋጅ፣ ምቾትና ፍጥነት በሌላቸው አነስተኛና ያረጁ ጀልባዎች የትራንስፖርት አገልግሎት ሲሰጥ መቆየቱን አስታውሰዋል።
አዲሷ ጀልባ ፈጣን፣ ዘመናዊና ምቾት ያላት በመሆኗ በርካታ ጎብኚዎች ጀልባዋን ለመጠቀም ጥያቄ እያቀረቡ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ሌላው በአስጎብኚነት ሥራ የተሰማሩት አቶ አበባው ሲሳይ በበኩላቸው፤ ከዚህ ቀደም በርካታ ጎብኚዎች በአንድ ጊዜ ሲመጡ ለማስተናገድ ይቸገሩ እንደነበር አስታውሰዋል።
የነበሩ ጀልባዎች አነስተኛና ውስን ሰው ብቻ እንደሚይዙ ጠቁመው፤ ጣናነሽ ቁጥር-ሁለት ጀልባ ብዛት ያለው ሰው የመያዝ አቅም ስላላት ችግሩ መፈታቱን ተናግረዋል።

ጀልባዋ ለጉዞ የሚያስፈልጉ ግብአቶች የተሟላላት በመሆኑ የጎብኚዎችን ቀልብ የመሳብ አቅሟም ከፍተኛ ነው ብለዋል።
አቶ ኤፍሬም አብርሀም የተባሉ ሌላው አስጎብኚ፤ የጀልባዋ ስራ መጀመር በጣና ሐይቅ ለሚከናወነው የቱሪዝም ሥራ አዲስ መነቃቃት እየፈጠረ መምጣቱን ተናግረዋል።
ሐይቁ የታሪካዊ፣ ሃይማኖታዊና ባህላዊ መስህብ ሃብት መገኛ በመሆኑ ይህን ዘርፍ ለኢኮኖሚያዊ ጥቅም ለማዋል የጀልባዋ ሥራ መጀመር ፋይዳው የጎላ ነው ብለዋል።
ከጅቡቲ ወደ ኢትዮጵያ አፋር ክልልና አዲስ አበባ አድርጋ ጠመዝማዛና አስቸጋሪውን የዓባይ በረሃን መንገድ በማቋረጥ ባሕር ዳር ከተማ የደረሰችው ጣናነሽ ቁጥር- ሁለት ጀልባ በኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርት እና ሎጀስቲክ አገልግሎት ድርጅት የተገዛች ናት።
ቀደም ሲል አገልግሎት ሲሰጡ ከቆዩት ጀልባዎች በዘመናዊነቷ ፣ በተገጠመላት ቴክኖሎጂ ፣ በፍጥነቷና ለጎብኚዎች ባላት ምቾት ለየት ያለች እንደሆነ ተመላክቷል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025