🔇Unmute
ደብረ ማርቆስ ፤ሕዳር 10/2018 (ኢዜአ)፡- በምስራቅ ጎጃም ዞን በበጀት ዓመቱ አራት ወራት ከ1 ነጥብ 6 ሚሊየን ኪሎ ግራም በላይ የማር ምርት ማምረት መቻሉን የዞኑ እንስሳትና አሳ ሃብት መምሪያ ገለጸ።
በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የሌማት ትሩፋት እና ሌሎችም ኢንሸቲቮች ተግባራዊ እየተደረጉ ውጤትም እየተመዘገበባቸው ይገኛል።
የምስራቅ ጎጃም ዞን እንስሳትና አሳ ሃብት መምሪያ የንብና ሃር ልማት ባለሙያ አቶ ስማቸው ዳምጤ ለኢዜአ እንደገለጹት፤በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን የአካባቢውን ምቹነት በመጠቀም የንብ ማነብ ስራ በብዛትና በስፋት እየተከናወነ እና ውጤትም እየተገኘ ነው፡፡
በዚህም መሰረት በተያዘው በጀት ዓመት ከሁለት ነጥብ አንድ ሚሊየን ኪሎ ግራም በላይ የማር ምርት ለማምረት ታቅዶ እስካሁን ከ1 ነጥብ 6 ሚሊየን ኪሎ ግራም በላይ ማምረት መቻሉን ገልጸዋል።
በዘርፉ ልማት አሁን ላይ ከ11 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች በተደራጀ መልኩ እየሰሩ መሆኑን አንስተው በዚህም ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ከአንድ ዘመናዊ ቀፎ በአማካይ 30 ኪሎ ግራም፣ ከሽግግር ቀፎ 18 ኪሎ ግራም ከባህላዊ ቀፎ ደግሞ 8 ኪሎ ግራም የማር ምርት እየተገኘ መሆኑን ገልጸዋል።
በዞኑ አዋበል ወረዳ አነቢ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር የሻንበል እውነቱ እና በጎዛምን ወረዳ የአጭራ ቀበሌ ነዋሪ ወይዘሮ ነጠሩ አዘነ፤ በዘርፉ ልማት ተጠቃሚ ስለመሆናቸው ተናግረዋል።
በአረንጓዴ ልማት የተራቆቱ አካባቢዎች በመልማታቸው እንዲሁም ዘመናዊ የንብ ማነብ አሰራር ተግባራዊ ማድረጋቸው በዘርፉ ልማት ስኬታማ ስለመሆናቸው አንስተዋል።
በመሆኑም ሌሎች አርሶ አደሮችም ከግብርና ስራቸው በተጓዳኝ በንብ ማነብ ስራ ቢሰማሩ አትራፊ እና ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ምክራቸውን ለግሰዋል።
በምስራቅ ጎጃም ዞን አሁን ላይ ከ160 ሺህ በላይ የንብ ቀፎዎች በምርት ስራ ላይ መሆናቸውን ከመምሪያው የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026