የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የኢትዮ-ማሌዢያ ከፍተኛ የቢዝነስ ፎረም በአዲስ አበባ መካሄድ ጀመረ

Nov 20, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሕዳር 10/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያና ማሌዢያ ከፍተኛ የቢዝነስ ፎረም በአዲስ አበባ አዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄድ ጀመረ።

በከፍተኛ የቢዝነስ ፎረሙ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርሃኑ ጸጋዬን ጨምሮ የሀገራቱ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣የንግድና ኢንቨስትመንት አልሚ ባለሃብቶች ተገኝተዋል።


በሀገራቱ ከፍተኛ የቢዝነስ ፎረም ላይ የኢትዮጵያ የንግድና ኢንቨስትመንት ጸጋዎች አዋጭነቶችን የሚያመላክቱ የመነሻ ጽሑፎች እየቀረቡ ይገኛል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለማሌዢያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሴሪ አንዋር ኢብራሂም በቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ተገኝተው ደማቅ አቀባበል ማድረጋቸው ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.