የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በመንግስት የተያዙ የልማት እቅዶች ግባቸውን እንዲመቱ ሁለንተናዊ ርብርብ ማድረግ ይገባል

Nov 20, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ ፤ሕዳር 10/2018 (ኢዜአ)፡- በመንግስት የተያዙ የልማት እቅዶች ግባቸውን እንዲመቱ ሁለንተናዊ ርብርብ ማድረግ እንደሚገባ የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ገለጹ።

10ኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም "የከተሞች ዕድገት ለኢትዮጵያ ልህቀት" በሚል መሪ ቃል በአፋር ክልል ሰመራ ሎጊያ ሲካሄድ ቆይቷል።

በዛሬው እለትም የፎረሙ የማጠቃለያ መርሀግብር ተካሂዷል።


በመድረኩ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፣የአፋር ክልል ርእሰ መስተዳድር አወል አርባ፣የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ እንዲሁም ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች ታድመዋል።

የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥የኢትዮጵያ ከተሞች በመንግስት የተቀየሰውን የኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ ለማሳካት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ትልቅ ተልዕኮ ተሰጥቷቸዋል።

የተጀመረውን ፈጣን የብልጽግና ጉዞ በማስቀጠል የዜጎችን ፍትሃዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ሥርዓት ለመገንባት የሚያስችል የ10 ዓመት መሪ ዕቅድ ላይ ተመስርቶ የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

በሁሉም የልማት መስኮች ውጤት ለማስመዝገብ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

እንደ ሀገር ተግባራዊ ለማድረግ የተቀረጹ ሥራዎችን ለማሳለጥ የሚያግዙ በርካታ የሕግ ማዕቀፎች ተቀርፀው ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን እና ተጨባጭ ለውጦችም መታየት መጀመራቸውን ጠቁመዋል፡፡

በፌደራልና በክልል እንዲሁም በክልል እና በከተሞች መካከል ያለው የዕቅድ መናበብና ቅንጅታዊ አሰራር ከጊዜ ወደ ጊዜ በላቀ ደረጃ መሻሻል እያሳየ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡


እነዚህን ሁኔታዎች በቀጣይም ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸው፥ የብልጽግና ዕቅድ በውጤታማነት ለማጠናቀቅ ከመቼውም በላቀ ሁኔታ መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡

የከተሞች ፎረም ከተሞችና አጋሮቻቸው የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎቻቸውን በማስተዋወቅ እውቅና እንዲያገኙና ተሞክሮዎቻቸውን እንዲለዋወጡ ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ተናግረዋል።

እንዲሁም በከተሞች መካከል ጤናማ የውድድር መንፈስ እንዲኖር በማድረግ ለኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል ብለዋል።

ባለፉት ዘጠኝ ዙሮች እየተካሄደ ባለው የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም ዝግጅቶች ከተሞች በበዓሉ ያላቸው የነቃ ተሳትፎ እያደገ መምጣቱን ጠቁመዋል።

በከተሞች እታየ ያለውን የልማትና የመልካም አስተዳደር መነቃቃት በላቀ ደረጃ ለማስቀጠል ሰፊ የሕዝብ ንቅናቄ ማቀጣጠል እንደሚገባ አመላክተዋል።

ከተሞች ያላቸውን የገቢ አማራጮች በአግባቡ በመለየት መሰብሰብና የከተማውን ህብረተሰብ የልማት ጥያቄ በአግባቡ ለመመለስ መስራት እንዳለባቸው አንስተዋል።

የሕብረተሰቡን ገቢ ለማሻሻል፣ ድህነትን ለመቀነስ እንዲሁም ፍትሐዊ የሀብት ክፍፍል እንዲፈጠር ለማድረግ ጠንካራ ስራ መስራት እንደሚገባ አመላክተዋል፡፡

በተጨማሪ የከተሞችን የምግብ ዋስትና ችግሮችን በማጥናት እና ለምግብ ዋስትና ችግር ተጋላጭ የሆኑትን የህብረተሰብ ክፍሎች በተለይ ወጣቶች፣ ሴቶች፣ አካል ጉዳተኞች ላይ ትኩረት ማድረግ እንደሚገባ አመላክተዋል፡፡


ሌላው በትኩረት ርብርብ ሊደረግበት የሚገባው የአገልግሎት አሰጣጥ ቀልጣፋነት መሆኑን አንስተዋል።

በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ያለውን እሮሮ ከከተማው ሕብረተሰብ ጋር በመሆን መፍታት እና ቀጣይ መፍትሔ እያስቀመጡ ወደፊት መጓዝ እንደሚገባ አመላክተዋል።

መላው የከተማ ነዋሪ በፖሊሲዎች፣ ስትራቴጂዎች እና ዕቅዶች ዙሪያ የተሟላ ግልጽነት ይዞ ከመንግስት መዋቅር ጋር እንዲሰራ ግንዛቤ መፍጠር እንደሚገባ ጠቁመዋል።

የመሬት አስተዳደር ሥርዓት ኋላቀር ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በዘርፉ የተንሰራፋው የመልካም አስተዳደር እጦትና ያልተገባ ጥቅም የመፈለግ አስተሳሰብ መኖሩን ጠቁመዋል።

በቀጣይም የከተሞች ተሞክሮ ተቀምሮ ወደ ሌሎች ከተሞች እንዲስፋፋ እንደሚደረግ አመላክተዋል።

ለፎረሙ ስኬት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026