🔇Unmute
ጅግጅጋ፤ ህዳር 11/2018 (ኢዜአ)፦ በሌማት ትሩፋት ውስን ቦታን በማልማት የአመጋገብ ሥርዓታቸውን ከማሻሻል ባለፈ የሥራ ባህላቸውን እየለወጡ መሆናቸውን በጅግጅጋ ከተማ የመርሃግብሩ ተሳታፊዎች ተናገሩ።
የሌማት ትሩፋት መርሃግብር በውስን ቦታ ላይ አትክልትና ፍራፍሬን እንዲሁም እንስሳትና የእንስሳት ተዋጽኦን በዘመነ መንገድ በማልማት ማዕዱን ምሉዕ ከማድረግ ባለፈ የአመጋገብ ስርዓቱን ለማሻሻል እንዲያስችል ታስቦ የተተገበረ ነው።
በዚህ መርሃ ግብርም በከተማም ሆነ በገጠሩ የአገሪቷ ክፍሎች በዘርፉ የተሰማሩ ሰዎች አትክልትና ፍራፍሬን ጨምሮ በእንስሳትን ተዋጽኦ ስራ ላይ በመሰማራት ከራሳቸው አልፈው ለገበያ ማረጋጋት የድርሻቸውን እየተወጡ መሆናቸው ታውቋል።
የጅግጅጋ ከተማ ነዋሪዎችም በእንስሳት፣ በአትክልትና ፍሬፍሬ እንዲሁም በሌሎች የከተማ ግብርና ዘርፎች ላይ በመሰማራት ተጠቃሚ በመሆን ላይ ይገኛሉ።
በከተማው በዘርፉ ከተሰማሩ ነዋሪዎች መካከል አቶ ከድር ዓሊ አንዱ ሲሆኑ በሌማት ትሩፋት መርሃግብር ባላቸው አነስተኛ መሬት ሥራ መጀመራቸውን ተናግረዋል።
በጓሮአቸው ያላቸውን ውስን ቦታን በአግባቡ ተጠቅመው የተለያዩ የአትክልት አይነቶች በማምረት ከራሳቸው አልፎ ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ወይዘሮ ፋጡማ አደን በበኩላቸው በሌማት ትሩፋት መርሃግብር የጓሮ አትክልት በማምረት ቤተሰባቸውን በተሟላ ማዕድ ከመመገብ አልፈው ለገበያ እንደሚያቀርቡ ገልጸዋል።
በተለይም ቆስጣ፣ ሰላጣ፣ ቃሪያና ሌሎችንም በማምረት ተጠቃሚ እንደሆኑ ገልጸው፤ ሌሎችም ውስን ቦታ ያላቸው ሰዎች የእሳቸውን አርአያ ተከትለው አልምተው ተጠቃሚ እንዲሆኑ መክረዋል።
ከዕለት ሥራቸው ጎን ለጎን በሌማት ትሩፋት መርሃግብር የጓሮ አትክልት በማልማት ገቢያቸውን እያሳደጉ መሆናቸውን የተናገሩት ደግሞ አቶ አብዲ ቼህ ናቸው።
አቶ አብዲ እንደሚሉት በአቅራቢያ ያሉትን የውሃ አማራጮችን በአግባቡ በመጠቀም ባላቸው ጓሮ ላይ ውጤታማ ስራ መስራት ችለዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026