🔇Unmute
ጅግጅጋ፤ ህዳር 11/2018 (ኢዜአ)፦ በሌማት ትሩፋት ውስን ቦታን በማልማት የአመጋገብ ሥርዓታቸውን ከማሻሻል ባለፈ የሥራ ባህላቸውን እየለወጡ መሆናቸውን በጅግጅጋ ከተማ የመርሃግብሩ ተሳታፊዎች ተናገሩ።
የሌማት ትሩፋት መርሃግብር በውስን ቦታ ላይ አትክልትና ፍራፍሬን እንዲሁም እንስሳትና የእንስሳት ተዋጽኦን በዘመነ መንገድ በማልማት ማዕዱን ምሉዕ ከማድረግ ባለፈ የአመጋገብ ስርዓቱን ለማሻሻል እንዲያስችል ታስቦ የተተገበረ ነው።
በዚህ መርሃ ግብርም በከተማም ሆነ በገጠሩ የአገሪቷ ክፍሎች በዘርፉ የተሰማሩ ሰዎች አትክልትና ፍራፍሬን ጨምሮ በእንስሳትን ተዋጽኦ ስራ ላይ በመሰማራት ከራሳቸው አልፈው ለገበያ ማረጋጋት የድርሻቸውን እየተወጡ መሆናቸው ታውቋል።
የጅግጅጋ ከተማ ነዋሪዎችም በእንስሳት፣ በአትክልትና ፍሬፍሬ እንዲሁም በሌሎች የከተማ ግብርና ዘርፎች ላይ በመሰማራት ተጠቃሚ በመሆን ላይ ይገኛሉ።
በከተማው በዘርፉ ከተሰማሩ ነዋሪዎች መካከል አቶ ከድር ዓሊ አንዱ ሲሆኑ በሌማት ትሩፋት መርሃግብር ባላቸው አነስተኛ መሬት ሥራ መጀመራቸውን ተናግረዋል።
በጓሮአቸው ያላቸውን ውስን ቦታን በአግባቡ ተጠቅመው የተለያዩ የአትክልት አይነቶች በማምረት ከራሳቸው አልፎ ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ወይዘሮ ፋጡማ አደን በበኩላቸው በሌማት ትሩፋት መርሃግብር የጓሮ አትክልት በማምረት ቤተሰባቸውን በተሟላ ማዕድ ከመመገብ አልፈው ለገበያ እንደሚያቀርቡ ገልጸዋል።
በተለይም ቆስጣ፣ ሰላጣ፣ ቃሪያና ሌሎችንም በማምረት ተጠቃሚ እንደሆኑ ገልጸው፤ ሌሎችም ውስን ቦታ ያላቸው ሰዎች የእሳቸውን አርአያ ተከትለው አልምተው ተጠቃሚ እንዲሆኑ መክረዋል።
ከዕለት ሥራቸው ጎን ለጎን በሌማት ትሩፋት መርሃግብር የጓሮ አትክልት በማልማት ገቢያቸውን እያሳደጉ መሆናቸውን የተናገሩት ደግሞ አቶ አብዲ ቼህ ናቸው።
አቶ አብዲ እንደሚሉት በአቅራቢያ ያሉትን የውሃ አማራጮችን በአግባቡ በመጠቀም ባላቸው ጓሮ ላይ ውጤታማ ስራ መስራት ችለዋል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025