🔇Unmute
ደብረ ማርቆስ፤ ግንቦት 4/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ምስራቅ ጎጃም ዞን ለማእድን ዘርፉ የተሰጠው ትኩረት ተኪ ምርቶችን በማምረት የውጭ ምንዛሪን ለማዳን የራሱ የሆነ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን የዞኑ ማእድን ሃብት ልማት መምሪያ አስታወቀ።
የመምሪያው ኃላፊ የሻረግ መልሰው ለኢዜአ እንደገለጹት በሀገር በቀል ኢኮኖሚ ሪፎርም ውስጥ ልዩ ትኩረት ከተሰጣቸው አምስት ዘርፎች መካከል የማእድን ልማት አንዱ ነው።
በመሆኑም በዞኑ ያለውን የግራናይት፣ እብነበረድ፣ ጅብሰም፣ ሲልካ ሳንድ፣ የድንገይ ክሰል፣ ብረት፣ ጥቁር ድንጋይና ሌሎች ማእድናትን በማልማት ለስራ እድል ፈጠራና ኢኮኖሚያዊ እድገት ለማዋል ጥረቶች እየተደረጉ ነው ብለዋል።
በዚህም በበጀት ዓመቱ ከማእድን ሃብት ልማት ከ37 ሚሊየን ብር በላይ የሚያወጡ ተኪ ምርቶችን በማምረት የውጭ ምንዛሬን ለማዳን ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን አስታውቀዋል።
ባለፉት ዘጠኝ ወራትም ከ300 ሺህ ኩንታል በላይ ጅብሰምና የኖራ ድንጋይ በማምረት ከ68 ሚሊየን ብር በላይ የሚሆን ተኪ ምርት ማምረት ከጥፍ በላይ አፈፃፀም ማስመዝገብ መቻሉን አብራርተዋል።
ስራውን ለማሳካትም የድጋፍና ክትትል ስራዎችን ከማጠናከር ባለፈ ባህላዊና በአነስተኛ የማእድን ልማት ስራ ለተሰማሩ ወጣቶች የአመራረት ጥራት ላይ ስልጠና መሰጠቱን ጠቁመዋል።
የዘርፉን አቅም በማጠናከር ከ 2 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ወጣቶች የስራ እድል መፍጠር ተችሏል ነው ያሉት።
በዞኑ በማእድን ልማት ዘርፉ ተሰማርተው ኢኮኖሚያዊ አቅማቸውን ማሳደግ ከቻሉ ወጣቶች መካከል የአዋበል ወረዳ ነዋሪ ይግዛው ካሴ፤ በግንባታ ጠጠር ምርት ስራ ላይ በመሰማራት ገቢውን ለማሳደግ እንደቻለ ነው የሚናገረው
የደብረ ኤሊያስ ወረዳ ነዋሪው ወጣት ቢያድለው ምህረት በበኩሉ፤ ለኮንስትራክሽን ዘርፉ የሚሆን ማእድን ማውጣት ስራ በመሰማራት ሃብት ማፍራቱን ነው የሚናገረው።
በዞኑ በከፍተኛ ማእድን ልማት ዘርፍ ከ200 በላይ አልሚዎች ፈቃድ ወስደው ወደ ስራ የገቡ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 14ቱ ወደ ማምረት መሸጋገራቸውን ከመምሪያው የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025