የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በዞኑ ለማእድን ዘርፉ የተሰጠው ትኩረት ተኪ ምርቶችን ለማሳደግ ድርሻው ከፍተኛ ነው

May 12, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደብረ ማርቆስ፤ ግንቦት 4/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ምስራቅ ጎጃም ዞን ለማእድን ዘርፉ የተሰጠው ትኩረት ተኪ ምርቶችን በማምረት የውጭ ምንዛሪን ለማዳን የራሱ የሆነ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን የዞኑ ማእድን ሃብት ልማት መምሪያ አስታወቀ።

የመምሪያው ኃላፊ የሻረግ መልሰው ለኢዜአ እንደገለጹት በሀገር በቀል ኢኮኖሚ ሪፎርም ውስጥ ልዩ ትኩረት ከተሰጣቸው አምስት ዘርፎች መካከል የማእድን ልማት አንዱ ነው።

በመሆኑም በዞኑ ያለውን የግራናይት፣ እብነበረድ፣ ጅብሰም፣ ሲልካ ሳንድ፣ የድንገይ ክሰል፣ ብረት፣ ጥቁር ድንጋይና ሌሎች ማእድናትን በማልማት ለስራ እድል ፈጠራና ኢኮኖሚያዊ እድገት ለማዋል ጥረቶች እየተደረጉ ነው ብለዋል።

በዚህም በበጀት ዓመቱ ከማእድን ሃብት ልማት ከ37 ሚሊየን ብር በላይ የሚያወጡ ተኪ ምርቶችን በማምረት የውጭ ምንዛሬን ለማዳን ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን አስታውቀዋል።

ባለፉት ዘጠኝ ወራትም ከ300 ሺህ ኩንታል በላይ ጅብሰምና የኖራ ድንጋይ በማምረት ከ68 ሚሊየን ብር በላይ የሚሆን ተኪ ምርት ማምረት ከጥፍ በላይ አፈፃፀም ማስመዝገብ መቻሉን አብራርተዋል።

ስራውን ለማሳካትም የድጋፍና ክትትል ስራዎችን ከማጠናከር ባለፈ ባህላዊና በአነስተኛ የማእድን ልማት ስራ ለተሰማሩ ወጣቶች የአመራረት ጥራት ላይ ስልጠና መሰጠቱን ጠቁመዋል።

የዘርፉን አቅም በማጠናከር ከ 2 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ወጣቶች የስራ እድል መፍጠር ተችሏል ነው ያሉት።

በዞኑ በማእድን ልማት ዘርፉ ተሰማርተው ኢኮኖሚያዊ አቅማቸውን ማሳደግ ከቻሉ ወጣቶች መካከል የአዋበል ወረዳ ነዋሪ ይግዛው ካሴ፤ በግንባታ ጠጠር ምርት ስራ ላይ በመሰማራት ገቢውን ለማሳደግ እንደቻለ ነው የሚናገረው

የደብረ ኤሊያስ ወረዳ ነዋሪው ወጣት ቢያድለው ምህረት በበኩሉ፤ ለኮንስትራክሽን ዘርፉ የሚሆን ማእድን ማውጣት ስራ በመሰማራት ሃብት ማፍራቱን ነው የሚናገረው።

በዞኑ በከፍተኛ ማእድን ልማት ዘርፍ ከ200 በላይ አልሚዎች ፈቃድ ወስደው ወደ ስራ የገቡ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 14ቱ ወደ ማምረት መሸጋገራቸውን ከመምሪያው የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026