የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በደቡብ ወሎ ዞን በተያዘው የመኸር እርሻ ከ224 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በስንዴ ይለማል

Jun 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደሴ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):-በደቡብ ወሎ ዞን በምግብ ራስን ለመቻልና የኢንዱስትሪ ግብአት አቅርቦትን ለማሳደግ በመኸር እርሻ ከ224 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በስንዴ እንደሚለማ የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

በመምሪያው የሰብል ልማት ቡድን መሪ አቶ ይመር ሰይድ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ ዞኑ ለስንዴ ሰብል ልማት ምቹ በመሆኑ በተያዘው የመኸር እርሻ ስንዴን በስፋት ለማልማት ዝግጅት ተደርጓል።

በዚህም በክረምቱ ከ224 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በስንዴ በማልማት ከ9 ነጥብ 9 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ሥራ ተገብቷል ብለዋል።


የስንዴ ልማት ምርታማነትን ለማሳደግም ከ400 ሺህ ኩንታል በላይ ሰው ሰራሽ ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ እየተሰራጨ መሆኑንም ገልጸዋል።

ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ለስንዴ ልማት የተሰጠው ትኩረት አርሶ አደሩን ውጤታማ ከማድረግ ባለፈ በምግብ ራሱን ለመቻልና ለኢንዱስትሪ የሚሆን ግብአት እንዲያቀርብ ማስቻሉንም ተናግረዋል።

ስንዴን በሜካናይዜሽን፣ በኩታ ገጠም እና በአዳዲስ አሰራሮች ታግዞ ማምረት መቻሉ እየተገኘ ላለው ውጤት መሰረት መሆኑንም አመልክተዋል።

በዞኑ ጀማ ወረዳ የቀበሌ 08 ነዋሪ አርሶ አደር እንድሪስ አበበ በሰጡት አስተያየት እንዳሉት፣ ሁለት ሄክታር መሬታቸውን በስንዴ ለማልማት ማሳቸውን ደጋግመው በማረስ ለዘር ሥራ አዘጋጅተዋል።

በግብርና ባለሙያዎች ድጋፍ ታግዘው በማልማትና የሰብል እንክብካቤ ሥራ በማከናወን እስከ 90 ኩንታል ምርት ለማግኘት ማቀዳቸውንም ገልጸዋል።

በዘንድሮው የመኸር ወቅት አንድ ሄክታር ተኩል ማሳቸው ላይ ስንዴ ለማልማት እንደተዘጋጁ መሆኑን የገለጹት ደግሞ በወረኢሉ ወረዳ የቀበሌ 04 ነዋሪ አርሶ አደር አህመድ ታደሰ ናቸው።

ቀደም ሲል ለስንዴ ልማት ብዙም ትኩረት እንደማይሰጡ አስታውሰው፣ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ስንዴን ማልማት ባህል በማድረጋቸው ተጠቃሚነታቸው እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል።

ባለፈው ዓመት በመኸር ወቅት በስንዴ ከለማው 200 ሺህ ሄክታር መሬት ከ6 ነጥብ 3 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱን ለማወቅ ተችሏል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቦንጋ ከተማን እድገትና ልማት በማፋጠን ለነዋሪቿ ምቹ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው 

ቦንጋ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- የቦንጋ ከተማን ዕድገትና ልማት በማፋጠን ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የካፋ ዞን አስ...

Jun 29, 2026

በክልሉ በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለሚሰማሩ ባለሀብቶች የሚደረጉ ማበረታቻዎች አመርቂ ውጤት አምጥተዋል -ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

አገና፤ ሰኔ 8/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለሚሰማሩ ባለሀብቶች የሚደረጉ ማበረታቻዎች አመርቂ ውጤት ማምጣታቸውን የ...

Jun 16, 2026

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026