🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ሰኔ 22/2018 (ኢዜአ)፦የሳዑዲ አረቢያ የተለያዩ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ለመሠማራት ፍላጎት እንዳላቸው አስታወቁ።
በሳዑዲ አረቢያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ምክትል የሚሲዮን መሪ አምባሳደር አወል ወግሪስ ሙሃመድ የተመራ ከፍተኛ ዲፕሎማሲያዊ ልዑካን ቡድን በደማም ሁለተኛ የኢንዱስትሪ ከተማ የሚገኙትን ጆ ድሪንክስ (Jo Drinks Factory) እና ሶይል ሮስተርስ (Soil Roadsters) ፋብሪካዎችን ጎብኝቷል።
በጉብኝቱ ወቅት አምባሳደር አወል ለኩባንያዎቹ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ፣የኢንቨስትመንት ፖሊሲዎች እና የተቀናጁ የአግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮችን (IAIPs) አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል።

የጆ ድሪንክስ ኩባንያ ከአልኮል ነፃ የሆኑ መጠጦችን አምራች ሲሆን፣ ኩባንያው በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋዩን ለማፍሰስና ምርቶቹን ለአገር ውስጥ እና ለውጭ ገበያ ለማቅረብ ፍላጎት እንዳለው አስታውቋል።
ሶይል ሮስተርስ ኩባንያ ከኢትዮጵያ የጉጂ፣ ጨልጨሌ፣ ሲዳማ ቦንቤ እና ይርጋጨፌ ልዩ ቡናዎችን (Specialty Coffee) እያስመጣ የሚቆላው ፋብሪካው፤ በቀጣይ በቀጥታ ከኢትዮጵያ አምራቾችና ማህበራት ለመግዛት መወሰኑን ገልጿል።
አምባሳደር አወል ወግሪስ የሁለቱ ኩባንያዎች መሪዎች በኢትዮጵያ የቅድመ-ኢንቨስትመንት ጉብኝት እንዲያደርጉ ጋብዘዋል።
በሪያድ የሚገኘው ኤምባሲ ለጉብኝቱ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ እንደሆነ ገልጸዋል።

ጉብኝቱ የኢትዮጵያ እና ሳዑዲ አረቢያ ግብርና ኢንዱስትሪን ጨምሮ በንግዱ ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማሳደግ የሚያስችል መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
ቦንጋ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- የቦንጋ ከተማን ዕድገትና ልማት በማፋጠን ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የካፋ ዞን አስ...
Jun 29, 2026
አገና፤ ሰኔ 8/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለሚሰማሩ ባለሀብቶች የሚደረጉ ማበረታቻዎች አመርቂ ውጤት ማምጣታቸውን የ...
Jun 16, 2026
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026