የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የሳዑዲ አረቢያ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ለመሠማራት ያላቸውን ፍላጎት ገለጹ

Jun 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሰኔ 22/2018 (ኢዜአ)፦የሳዑዲ አረቢያ የተለያዩ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ለመሠማራት ፍላጎት እንዳላቸው አስታወቁ።

በሳዑዲ አረቢያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ምክትል የሚሲዮን መሪ አምባሳደር አወል ወግሪስ ሙሃመድ የተመራ ከፍተኛ ዲፕሎማሲያዊ ልዑካን ቡድን በደማም ሁለተኛ የኢንዱስትሪ ከተማ የሚገኙትን ጆ ድሪንክስ (Jo Drinks Factory) እና ሶይል ሮስተርስ (Soil Roadsters) ፋብሪካዎችን ጎብኝቷል።

በጉብኝቱ ወቅት አምባሳደር አወል ለኩባንያዎቹ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ፣የኢንቨስትመንት ፖሊሲዎች እና የተቀናጁ የአግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮችን (IAIPs) አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል።


የጆ ድሪንክስ ኩባንያ ከአልኮል ነፃ የሆኑ መጠጦችን አምራች ሲሆን፣ ኩባንያው በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋዩን ለማፍሰስና ምርቶቹን ለአገር ውስጥ እና ለውጭ ገበያ ለማቅረብ ፍላጎት እንዳለው አስታውቋል።

ሶይል ሮስተርስ ኩባንያ ከኢትዮጵያ የጉጂ፣ ጨልጨሌ፣ ሲዳማ ቦንቤ እና ይርጋጨፌ ልዩ ቡናዎችን (Specialty Coffee) እያስመጣ የሚቆላው ፋብሪካው፤ በቀጣይ በቀጥታ ከኢትዮጵያ አምራቾችና ማህበራት ለመግዛት መወሰኑን ገልጿል።

አምባሳደር አወል ወግሪስ የሁለቱ ኩባንያዎች መሪዎች በኢትዮጵያ የቅድመ-ኢንቨስትመንት ጉብኝት እንዲያደርጉ ጋብዘዋል።

በሪያድ የሚገኘው ኤምባሲ ለጉብኝቱ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ እንደሆነ ገልጸዋል።


ጉብኝቱ የኢትዮጵያ እና ሳዑዲ አረቢያ ግብርና ኢንዱስትሪን ጨምሮ በንግዱ ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማሳደግ የሚያስችል መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026