🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦የብሔራዊ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የሀብት ልየታ ጥናት ውጤታማ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንትን ለማጠናከር እንደሚያስችል የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል ገለጹ።
ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነውን የብሔራዊ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የሀብት ልየታ ጥናት ትግበራ መርሃ-ግብር እያካሄደ ይገኛል።

በመድረኩ ላይ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች እና ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
በመርሃ-ግብሩ መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል፤ ለሀገራት ልዕልና መለኪያው የማምረቻው ዘርፍ የደረሰበት ደረጃ መሆኑን ገልጸዋል።
በመሆኑም በኢትዮጵያ ለዘርፉ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ በመሠራቱ ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ እንደሚገኝ አስገንዝበዋል።
በተለይም በ"ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ በማምረቻው ዘርፍ በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን ያነሱት ሚኒስትሩ፤ ዘርፉ ለሀገር ውስጥ ጠቅላላ ምርት ያለው ድርሻ ማደጉን፣ ገቢ ምርቶችን የመተካት ሂደት መሻሻሉን እና የኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅም ማደጉን ጠቅሰዋል።

አሁን ይፋ የተደረገው የብሔራዊ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የሀብት ልየታ ጥናት በሀገር አቀፍ ደረጃ በየአካባቢው የሚገኙ እምቅ ሀብቶችን፣ መሠረተ ልማቶችን እና ሌሎች ለኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታዎችን የተሟላ መረጃ የሚሰጥ መሆኑን አብራርተዋል።
ይህ የተሟላ መረጃ ደግሞ በእውቀት ላይ የተመሠረተ ኢንቨስትመንትን ለማሳደግ ጉልህ ሚና ይኖረዋል ብለዋል።
ጥናቱ ወደፊት ለሚከናወኑ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴዎች ትክክለኛውን አቅጣጫ የሚያመላክት ከመሆኑም በላይ፣ አዳዲስ ኢንቨስትመንቶችን በስፋት ለመሳብ ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ጨምረው ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦የብሔራዊ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የሀብት ልየታ ጥናት ውጤታማ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንትን ለማጠናከር እንደሚያስችል የኢ...
Jul 8, 2026
ቦንጋ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- የቦንጋ ከተማን ዕድገትና ልማት በማፋጠን ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የካፋ ዞን አስ...
Jun 29, 2026
አገና፤ ሰኔ 8/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለሚሰማሩ ባለሀብቶች የሚደረጉ ማበረታቻዎች አመርቂ ውጤት ማምጣታቸውን የ...
Jun 16, 2026
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026