🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ በበጀት ዓመቱ ከአምስት ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ያስቻለ አቅም መገንባቱን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ በመገኘት፣ የ2018 በጀት ዓመት የመንግሥትን አፈጻጸም በተመለከተ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው፤ የ2018 በጀት ዓመት ከሌላው ጊዜ በተለየ መልኩ በከፍተኛ ደረጃ ለዜጎች በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገር በስፋት የሥራ ዕድል የተፈጠረበት ስኬታማ ዓመት መሆኑን አስታውቀዋል።
መንግሥት የሥራ አጥነትን ችግር ለመቅረፍ ባከናወናቸው ዘርፈ-ብዙ ተግባራት በአጠቃላይ ከ5 ሚሊዮን በላይ ለሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር የሚያስችል አቅም መገንባቱን ገልጸዋል፡፡
በዚህ በጀት ዓመት በሀገር ውስጥ 4 ነጥብ 9 ሚሊዮን ለሚሆኑ ዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል መፈጠሩን ጠቅሰው በውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ከ600 ሺህ በላይ ዜጎች የሥራ ዕድል እንዲያገኙ መደረጉን ተናግረዋል፡፡
የዲጂታል ዕድሎችን በመጠቀም ወደ 40 ሺህ የሚጠጉ ዜጎችን በርቀት የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ጠቁመዋል፡፡
ኢትዮጵያ ለዜጎቿ አስተማማኝ የሥራ ዕድል መፍጠር የሚችል ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባት፣ በብዝሃ ኢኮኖሚ ዘርፎች ላይ የሰራቻቸው አበረታችና ስልታዊ ሥራዎች ውጤት መሆኑን አብራርተዋል።
ነገ ከዚህ የተሻለ ከፍተኛ የስኬት ደረጃ ላይ ለመድረስ ግን ዜጎች ለሥራ ያላቸውን ባህል መቀየርና መትጋት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል።
በተለይም ወጣቶች ወጣ ብለው የመሥራትና የመንቀሳቀስ ልምዳቸውን ሊያጠናክሩ እንደሚገባም መክረዋል፡፡
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦የብሔራዊ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የሀብት ልየታ ጥናት ውጤታማ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንትን ለማጠናከር እንደሚያስችል የኢ...
Jul 8, 2026
ቦንጋ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- የቦንጋ ከተማን ዕድገትና ልማት በማፋጠን ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የካፋ ዞን አስ...
Jun 29, 2026
አገና፤ ሰኔ 8/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለሚሰማሩ ባለሀብቶች የሚደረጉ ማበረታቻዎች አመርቂ ውጤት ማምጣታቸውን የ...
Jun 16, 2026
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026