የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በበጀት ዓመቱ ከአምስት ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ያስቻለ አቅም ተገንብቷል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

Jul 8, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ በበጀት ዓመቱ ከአምስት ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ያስቻለ አቅም መገንባቱን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ በመገኘት፣ የ2018 በጀት ዓመት የመንግሥትን አፈጻጸም በተመለከተ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው፤ የ2018 በጀት ዓመት ከሌላው ጊዜ በተለየ መልኩ በከፍተኛ ደረጃ ለዜጎች በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገር በስፋት የሥራ ዕድል የተፈጠረበት ስኬታማ ዓመት መሆኑን አስታውቀዋል።

መንግሥት የሥራ አጥነትን ችግር ለመቅረፍ ባከናወናቸው ዘርፈ-ብዙ ተግባራት በአጠቃላይ ከ5 ሚሊዮን በላይ ለሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር የሚያስችል አቅም መገንባቱን ገልጸዋል፡፡

በዚህ በጀት ዓመት በሀገር ውስጥ 4 ነጥብ 9 ሚሊዮን ለሚሆኑ ዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል መፈጠሩን ጠቅሰው በውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ከ600 ሺህ በላይ ዜጎች የሥራ ዕድል እንዲያገኙ መደረጉን ተናግረዋል፡፡

የዲጂታል ዕድሎችን በመጠቀም ወደ 40 ሺህ የሚጠጉ ዜጎችን በርቀት የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ጠቁመዋል፡፡

ኢትዮጵያ ለዜጎቿ አስተማማኝ የሥራ ዕድል መፍጠር የሚችል ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባት፣ በብዝሃ ኢኮኖሚ ዘርፎች ላይ የሰራቻቸው አበረታችና ስልታዊ ሥራዎች ውጤት መሆኑን አብራርተዋል።

ነገ ከዚህ የተሻለ ከፍተኛ የስኬት ደረጃ ላይ ለመድረስ ግን ዜጎች ለሥራ ያላቸውን ባህል መቀየርና መትጋት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል።

በተለይም ወጣቶች ወጣ ብለው የመሥራትና የመንቀሳቀስ ልምዳቸውን ሊያጠናክሩ እንደሚገባም መክረዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026