የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ኢትዮጵያ በአለም ሶስተኛዋ ቡና ላኪ ሀገር ሆናለች-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

Jul 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ለቡና ልማት የተሰጠው ትኩረት ኢትዮጵያን በአለም ሶስተኛዋ ቡና ላኪ ሀገር እንድትሆን ማስቻሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገልጸዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ የ2018 በጀት ዓመት የመንግሥት አፈጻጸምን በተመለከተ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማብራሪያቸው፥ ሀገራዊ የሪፎርም ስራው ለውጭ ምንዛሬ ግኝት ስኬቶች ከፍተኛ አስተዋጽዎ ማበርከቱን ተናግረዋል።

በዚህም በዘንድሮው አመት የኢትዮጵያ ከሸቀጦች ኤክስፖርት 11 ቢሊዮን ዶላር በላይ መሆኑን ገልጸው፥ከቡና ኤክስፖርት ብቻ በአመቱ 3 ነጥብ 1 ቢሊዮን ዶላር ተገኝቷል ብለዋል።

ኢትዮጵያ የኮፊ አረቢካ መገኛ እንደመሆኗ በየትኛውም ዘመን ቡና ወደ ውጭ ስትልክ ቆይታለች ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥በእነዚህ አመታት ግን ይህ ነው የሚባል ገቢ ማግኘት አልቻለኝም።

በዚህም ሀገሪቱ ባለፉት 17 አመታት ቡናን ወደ ውጭ በመላክ ያገኘችው ገቢ 3 ነጥብ 3 ቢሊዮን ዶላር መሆኑን ገልጸዋል።

መንግስት ለቡና ልማት በሰጠው ከፍተኛ ትኩረት ግን በዘንድሮው አመት ብቻ 3 ነጥብ 1 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማሳካት መቻሉን ጠቁመዋል።

አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለቡና ኤክስፖርት እድገት ስኬት አስተዋጽዎ ማበርከቱን ገልጸው፤ በቡና ልማት ላይ የመጣውን ለውጥ በተጨባጭ የሚያሳይ ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አክለውም፥ቡናን ካልተከልን፤ካልተንከባከብን፤ካልለቀምን፤ ካላጠብን፤ካላሸግን እና ካላጓጓዝን ይህ ውጤት ሊመጣ አይችልም ብለዋል።

የኢትዮጵያን የሀገር ውስጥ የቡና ፍጆታ ከመቻል አልፈን ለውጭ ገበያ በማቅረብ የመጣው ለውጥ የሀገራዊ የሪፎርሙ ስኬት መገለጫም ነው ብለዋል።

ኢትዮጵያ በቡና ልማት እና ኤክስፖርት ላይ ያሳየችው እድገት በአሁኑ ሰዓት ከብራዚል እና ኮሎምቢያ ቀጥላ በአለም 3ተኛ ደረጃ እንድትይዝ አድርጓታል ሲሉ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የብሔራዊ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የሀብት ልየታ ጥናት ውጤታማ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንትን ለማጠናከር ያስችላል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦የብሔራዊ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የሀብት ልየታ ጥናት ውጤታማ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንትን ለማጠናከር እንደሚያስችል የኢ...

Jul 8, 2026

የቦንጋ ከተማን እድገትና ልማት በማፋጠን ለነዋሪቿ ምቹ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው 

ቦንጋ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- የቦንጋ ከተማን ዕድገትና ልማት በማፋጠን ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የካፋ ዞን አስ...

Jun 29, 2026

በክልሉ በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለሚሰማሩ ባለሀብቶች የሚደረጉ ማበረታቻዎች አመርቂ ውጤት አምጥተዋል -ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

አገና፤ ሰኔ 8/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለሚሰማሩ ባለሀብቶች የሚደረጉ ማበረታቻዎች አመርቂ ውጤት ማምጣታቸውን የ...

Jun 16, 2026

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026