🔇Unmute
ደሴ ፤ ሐምሌ 1/ 2018 (ኢዜአ):- በአማራ ክልል በዘመናዊ ግብርና የእንስሳት ሀብት ምርታማነትን በማሳደግ ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በምክትል ርዕስ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል የገጠር ክላስተር አስተባባሪ ድረስ ሳህሉ (ዶ/ር) ገለጹ።
የክልሉ ግብርና ቢሮ "ዘመናዊ ግብርና ለሁለንተናዊ ልዕልና" በሚል መሪ ሐሳብ ያዘጋጀው የምክክር መድረክ በደሴ ከተማ ተካሒዷል።

በምክትል ርዕስ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል የገጠር ክላስተር አስተባባሪ ድረስ ሳህሉ(ዶ/ር) እንደገለጹት፤የግብርናውን ዘርፍ በማዘመን ለወጭ ንግድና ለኢንዱስትሪ ግብአት የሚተርፍ ምርት ለማምረት ርብርብ እየተደረገ ነው።
በዚህም በዘመናዊ አሰራር፣ የምርት ማሳደጊያ ግብአት በመጠቀም፣ በሜካናይዜሽንና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በተለይ በክልሉ በቴክኖሎጂ የተደገፈ በዘመናዊ ግብርናና እንስሳት ሀብት ልማት የተጀመረው ስራ ምርታማነትን በማሳደግ ሁለተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ መሰረት እየሆነ መምጣቱን ተናግረዋል።
በአሁኑ ወቅትም በምርምር የታገዙ አዳዲስ የሰብል ዝርያዎችን ተግባራዊ በማድረግ ምርታማነትን ለማሳደግ የተከናወኑ ተግባራት የሚበረታቱ ናቸው ብለዋል።
አርሶ አደሩ የሚያገኘውን እርጥበት ተጠቅሞ ፈጥኖ የዘር ስራውን እንዲጀምር፣ ውሃ እንዲያሰባስብ ፣ ፈጥነው የሚደርሱና ድርቅን የሚቋቋሙ አዳዲስ የሰብል ዝርያዎችን እንዲጠቀም ማድረግ እንደሚያስፈልግ ነው ያመላከቱት ።
ለዚህም መንግስት ምርታማነትን ለማሳደግ ቴክኖሎጂና ግብዓቶችን በስፋት እያቀረበ እንደሚገኝም ገልጸዋል።

የአማራ ክልል እንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ጋሻው ሙጨ (ዶ/ር) በበኩላቸው ፤የእንስሳት ዝርያን በማሻሻል በጥራት እንዲመረት ከማድረግ አኳያ አበረታች የሆኑ ውጤቶች ተመዝግበዋል ብለዋል።
በተለይም በሌማት ትሩፋት የወተት፣ የስጋ ፣ የእንቁላል ፣ የማር ፣ የዓሳና የሌሎችንም ምርታማነት በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ዜጎች ጥሪት እንዲያፈሩ ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል ሲሉ ገልጸዋል።
የደቡብ ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ ምክትል ኃላፊ አቶ ደመቀ አድማሱ በበኩላቸው፣ በዞኑ በምርምር የወጡ አዳዲስ የሰብል ዝርያዎችን በመጠቀም ምርታማነትን ለማሳደግ ዝግጅት እየተደረገ ነው ብለዋል።

በተለይ ድርቅን የሚቋቋሙ፣ ምርታማና ፈጥነው የሚደርሱ ምርጥ ዘሮችን ለአርሶ አደሩ ለማቅረብ እንዲቻልም ሰፊ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
የሰሜን ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ተገኝ አባተ በበኩላቸው፣ በተሻሻለ አሰራርና ቴክኖሎጂን በመጠቀም የሰብል ምርታማነትን ለማሳደግ ዝግጅት መደረጉን ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦የብሔራዊ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የሀብት ልየታ ጥናት ውጤታማ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንትን ለማጠናከር እንደሚያስችል የኢ...
Jul 8, 2026
ቦንጋ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- የቦንጋ ከተማን ዕድገትና ልማት በማፋጠን ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የካፋ ዞን አስ...
Jun 29, 2026
አገና፤ ሰኔ 8/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለሚሰማሩ ባለሀብቶች የሚደረጉ ማበረታቻዎች አመርቂ ውጤት ማምጣታቸውን የ...
Jun 16, 2026
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026