የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በደቡብ ወሎ ዞን እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት የከተሞችን ገጽታ በመቀየር ለእንቅስቃሴና ለልማት ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል

Aug 10, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደሴ ፤ ነሐሴ 4/2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ወሎ ዞን እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት የከተሞችን ገጽታ በመቀየር እንዲነቃቁ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን የዞኑ ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ አስታወቀ።

በመምሪያው የመሰረተ ልማት ቡድን የኮንስትራክሽን አስተዳደር መሃንዲስ አደም መሃመድ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በሐይቅ፣ ጊምባ፣ መካነሰላም፣ ሀርቡ፣ ወረኢሉ፣ አቀስታ እና ደጎሎ ከተሞች የኮሪደር ልማት ስራ እየተካሔደ ነው።


በነዚሁ አካባቢዎች በመገንባት ላይ ካለው 6 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ሥራ ውስጥም ከሁለት ኪሎ ሜትር በላይ የሚሆነው ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት መሆኑን ተናግረዋል።


የኮሪደር ልማቱ ከተሞችን በማስዋብና ገጽታቸውን በመቀየር እንዲነቃቁ ከማድረጉ ባለፈ ለነዋሪዎች፣ ለኢንቨስትመንትና ለቱሪዝም ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ገልጸዋል።


ቀሪውን ሥራ በፍጥነትና በጥራት አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት ሰፊ ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝም አክለዋል።


ልማቱ የእግረኛና የብስክሌት መንገዶችን፣ መዝናኛዎችንና ሌሎች መሰረተ ልማቶችን ያካተተ በመሆኑ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ማድረጉን ነው የጠቀሱት።


ማሕበረሰቡ ለግንባታ ስራው በገንዘብ፣ በጉልበትና ቁሳቁስ በማቅረብ ከፍተኛ ተሳትፎ እያደረገ ይገኛል ብለዋል።


የሐይቅ ከተማ ነዋሪ ወይዘሮ እናትነሽ በሽር በበኩላቸው፤ የኮሪደር ልማቱ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት መደረጉ ከተማዋን ከማነቃቃቱ በላይ ለነዋሪዎች ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ገልጸዋል።


በተለይም የእግረኛ፣ የተሽከርካሪና የብስክሌት መንገዶችን እንዲሁም መዝናኛዎችን ማካተቱ የትራፊክ አደጋን በማስቀረት በነጻነት ለመንቀሳቀስ አስችሎናል ነው የሚሉት።


ሌላው የዚሁ ከተማ ነዋሪ ሸህ ጀማል ለይሱ፤ ልማቱ የከተማዋን ገጽታ በማሳመርና በማስዋብ ተጠቃሚ እንዳደረጋቸው ነው ያብራሩት።


ህብረተሰቡ በገንዘብ፣ በቁሳቁስና በጉልበት ያደረገው አስተዋጽኦ የግንባታ ስራው በፍጥነትና በጥራት ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ ማድረጉን ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026

የአየር ማረፊያው ለአገልግሎት መብቃት የአካባቢውን የንግድ፣ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ የሚያነቃቃ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 5 /2018 (ኢዜአ)፦የአየር ማረፊያው ለአገልግሎት መብቃትም የአካባቢውን የንግድ፣የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ በማ...

Jul 13, 2026

የኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ትብብርን ለማጠናከር ምቹ ምህዳር ፈጥሯል

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የተገበረችው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያና የዲጂታል አገልግሎት መስፋፋት የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ትብብርን ለማጠና...

Jul 9, 2026