🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የተገበረችው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያና የዲጂታል አገልግሎት መስፋፋት የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ትብብርን ለማጠናከር ምቹ ምህዳር መፍጠራቸውን ኢዜአ ያነጋገራቸው የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች ገለጹ።
በኢትዮጵያ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በብዝኃ ዘርፍ የኢኮኖሚ ዕድገት ከተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት መካከል ለንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፉ የተመቻቸ ምህዳር መፍጠር ይገኝበታል።
ይህንን ተከተሎም መንግሥት የተለያዩ እርምጃዎችን በመውሰዱ በሀገሪቱ የኢንቨስትመንት ፍሰት እየጨመረ ነው።
ኢዜአ ኢትዮጵያ ለውጭ ቀጥታ የኢንቨስትመንት የፈጠረችውን ምቹ ሁኔታ በተመለከተ የተለያዩ ሀገራትን አምባሳደሮችና ተወካዮችን አነጋግሯል።
በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አብርሃም ንጉሴ (ዶ/ር)፥ እስራኤልና ኢትዮጵያ የጠበቀ ኢኮኖሚያዊ ግንኙነት ያላቸው ሀገራት መሆናቸውን ገልጸዋል።
እስራኤል በኢትዮጵያ በተለያዩ የኢንቨስትመንትና የንግድ ዘርፎች ላይ በመሰማራት ለጋራ እድገት አበክራ እየሰራች እንደምትገኝ ተናግረዋል።
እስራኤል ከኢትዮጵያ ቡና፣ ሰሊጥና ሌሎች ምርቶች እንደምታስገባ ጠቅሰው፥ እስራኤልም ያላትን የቴክኖሎጂ አቅምና እውቀት ለኢትዮጵያ በማካፈል ላይ እንደምትገኝ አክለዋል።
ኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ተግባራዊ ማድረጓ እና ሀገሪቱ ወደ ዲጂታላይዜሽን የምታደርገው ፈጣን ግስጋሴ፣ በአሁኑ ሰዓት ለኢንቨስትመንት ምቹ ምህዳር ያላት ሀገር እንዳደረጋት ገልጸዋል፡፡
ይህም እስራኤል በኢትዮጵያ ያላትን ኢንቨስትመንት ይበልጥ እንድታስፋፋ ምቹ መደላድል እየፈጠረ መሆኑን ጨምረው አስታውቀዋል፡፡

በኢትዮጵያ የስሪላንካ አምባሳደር ኒርማላ ፓራናቪታና በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ በተለያዩ ዓለም አቀፍ እና ቀጣናዊ መድረኮች ለንግድና ለኢንቨስትመንት ዘርፍ ያላትን ምቹ ሁኔታዎች ለማስተዋወቅ የምታደርገውን ጥረት አድንቀዋል፡፡
እንዲሁም የምታቀርባቸው የተለያዩ ማበረታቻዎች ኢንቨስትመንትን በመሳብ ረገድ ትልቅ ሚና እንደሚጫወቱ አስታውቀዋል፡፡
ስሪላንካ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ በጨርቃ ጨርቅ ዘርፍ ላይ በስፋት ኢንቨስት እያደረገች እንደምትገኝ አንስተው፣ በቀጣይም በሌሎች አማራጭ የኢንቨስትመንት መስኮች ላይ ለመሰማራት ትልቅ ፍላጎትና ቁርጠኝነት እንዳላት ጠቅሰዋል፡፡
በኢትዮጵያ የፓኪስታን የንግድና ኢንቨስትመንት ጉዳዮች ተወካይ ባሲት ሳሊም ሻህ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ለንግድ ግንኙነትና ለኢንቨስትመንት እጅግ ምቹ የሆነ መልክዓ-ምድራዊ አቀማመጥ ያላት ሀገር መሆኗን ጠቅሰዋል።

ፓኪስታን በአሁኑ ወቅት የተወሰኑ የኢትዮጵያ የወጪ ንግድ ምርቶችን ወደ ሀገሯ እያስገባች መሆኑን የገለጹት ተወካዩ፤ ከእነዚህም መካከል ቡና እና ጥራጥሬ ተጠቃሽ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ፓኪስታን ወደ ሀገሯ ልታስገባቸው የምትፈልጋቸው ዘርፈ-ብዙ ሀብቶች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ጠቁመው፣ በቀጣይም ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የንግድና የኢንቨስትመንት ግንኙነት ይበልጥ ለማሳደግ በትኩረት እየሰራች መሆኑን ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ ውብ የቱሪዝም ጸጋዎችን የተቸረች ሀገር መሆኗን ገልጸው፥ ፓኪስታን ኢትዮጵያ ጋር በቱሪዝምና ሌሎች ዘርፎች ትብብርን ለማጠናከር ዝግጁ መሆኗን አረጋግጠዋል።
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የተገበረችው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያና የዲጂታል አገልግሎት መስፋፋት የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ትብብርን ለማጠና...
Jul 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦የብሔራዊ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የሀብት ልየታ ጥናት ውጤታማ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንትን ለማጠናከር እንደሚያስችል የኢ...
Jul 8, 2026
ቦንጋ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- የቦንጋ ከተማን ዕድገትና ልማት በማፋጠን ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የካፋ ዞን አስ...
Jun 29, 2026
አገና፤ ሰኔ 8/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለሚሰማሩ ባለሀብቶች የሚደረጉ ማበረታቻዎች አመርቂ ውጤት ማምጣታቸውን የ...
Jun 16, 2026