🔇Unmute
ወጣት አዝመራው ታደሰ የ 5 ሚሊየን ኢትዮጵያውያን ኮደሮች ኢኒሼቲቭ ተመራቂ ወጣት ባለሙያ ነው።
ወጣቱ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈትቤት በ5 ሚሊየን ኢትዮጵያውያን ኮደሮች ኢኒሼቲቭ ዙሪያ ባዘጋጀው የልምድ ልውውጥ መርሐ ግብር ላይ በመገኘት ተሞክሮውን አካፍሏል፡፡
ወጣት አዝመራው በመርሐ ግብሩ ላይ እንዳለው ፥ ይህንን ታላቅ ዕድል በዩኒቨርሲቲ ቆይታው የመጨረሻ ዓመታት ውስጥ በመቀላቀል አስደናቂ የስኬት ምዕራፍ ላይ ደርሷል።
ወጣቱ ኮድ ማድረግን መማር ከጀመረበት ጥረት ተነስቶ በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ ኮደሮችን የሚያገናኝ ድረ ገጽ ወደ ማበልጸግ መሸጋገር መቻሉንና ዛሬ ደግሞ ፉል ስታክ ድረ ገጽ አልሚ መሆኑን አስረድቷል።
በሰርተፍኬት ብቻ አትወሰኑ የሚለው ወጣት አዝመራው የተማራችሁትን በተግባር በማዋል እና በመለማመድ እውነተኛ ዕድገት ማምጣት ትችላላችሁ ሲል ተናግሯል።
በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ሥዩም እንዳሉት ፥ የወጣቶች የቴክኒክና የዲጂታል ክህሎት ብቃት ወሳኝ ሀገራዊ ሀብት ነው፡፡
በዚህ ክረምት የኮደሮችን ቁጥር 7 ሚሊየን ለማድረስ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የቀረበውን ጥሪ ተግባራዊነት አረጋግጠዋል።
ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...
Aug 10, 2026
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...
Jul 20, 2026
አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 5 /2018 (ኢዜአ)፦የአየር ማረፊያው ለአገልግሎት መብቃትም የአካባቢውን የንግድ፣የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ በማ...
Jul 13, 2026
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የተገበረችው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያና የዲጂታል አገልግሎት መስፋፋት የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ትብብርን ለማጠና...
Jul 9, 2026