የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የአርባ ምንጭ ኮንፈረንስ ሪዞርት የቱሪዝም ዘርፉን የሚያነቃቃና ለከተማዋም ተጨማሪ ድምቀት ነው

Aug 12, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አርባ ምንጭ፤ ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በገበታ ለትውልድ መርሐግብር የተገነባው የአርባ ምንጭ ኮንፈረንስ ሪዞርት የቱሪዝም ዘርፉን የሚያነቃቃና ለከተማዋም ተጨማሪ ድምቀት መሆኑ ተገለጸ።

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢኒሼቲቭ የተገነባውና የገበታ ለትውልድ ፕሮጀክት አካል የሆነው አርባ ምንጭ ኮንፈረንስ ሪዞርት በቅርቡ መመረቁ ይታወቃል።

ኢዜአ ያነጋጋራቸው የአርባ ምንጭ ከተማ ቱሪዝም መምሪያ ሃላፊ አቶ ደስታ ደምበላ እንደገለጹት ሪዞርቱ ለአካባቢው ብሎም ለሀገር ዘርፈ ብዙ ጥቅም ያለው ግዙፍ የልማት ፕሮጀክት ነው።


ሪዞርቱ የገበታ ለትውልድ ፕሮጀክት አካል መሆኑንም ጠቅሰው፣ የቱሪዝምና የአገልግሎት ዘርፉን ከማነቃቃት ባለፈ ለዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር አስተዋጾ እንደሚኖረው ተናግረዋል።

ሪዞርቱ የተገነባበት ቦታ ለቱሪዝም ምቹ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ደስታ፣ በተለይ በዓባያ ሐይቅ ላይ የተገነባው ተንሳፋፊ ሬስቶራንት የተለየ በመሆኑ የጎብኚዎችን ቀልብ ይስባል ብለዋል ።

እንደሃላፊው ገለጻ የአካባቢውን የቱሪዝም ፀጋዎች ይበልጥ እንዲታወቁ በማድረግ በኩልም ፋይዳው የጎላ ሲሆን ሀገራዊ ጠቀሜታም ከፍተኛ ነው ብለዋል።

የአርባ ምንጭ ከተማ ነዋሪው አፈወርቅ አለማየሁ በበኩላቸው እንዳሉት፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች በገበታ ለሀገርና ገበታ ለትውልድ ያስገነቧቸው ፕሮጀክቶች የሀገርን ገጽታ በመሰረታዊነት የቀየሩ ናቸው።


ሪዞርቱ በአርባ ምንጭና አካባቢው የሚገኘውን የሸማ ጥበብ፣ የባህል፣ የምግብና የአልባሳት ሥራዎችን ለማስተዋወቅና ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም ለማሳደግ ምቹ ዕድል ይፈጥራል ሲሉም አክለዋል።

በግንባታው ሂደት ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል መፈጠሩን አስታውሰው፣ በቀጣይም ለዜጎች በቋሚና በጊዜያዊነት ተጨማሪ የሥራ ዕድል ይፈጥራል ብለዋል።

ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ሙና ዮሐንስ ሪዞርቱ የከተማዋን ውበት አጉልቶ የሚያወጣ ተጨማሪ ፀጋ ነው ሲሉ ገልጸዋል።


ወጣት ታምራት በርገኔ በበኩሉ ሪዞርቱ የአርባ ምንጭ ከተማን ገጽታ ይበልጥ ከማድመቅ ባለፈ ቱሪስትን በመሳብ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳው የጎላ መሆኑን ገልፆ፣ ይህም ለከተማዋና ለሀገር እድገት የሚኖረው አበርክቶ የጎላ ነው ብሏል።


አስተያየት ሰጪዎቹ በአርባ ምንጭና አካባቢው ሰፊ የቱሪዝም አቅም በመኖሩ ሪዞርቱ ከሀገር ውስጥና ከውጭ ወደ ከተማዋ ለሚመጡ ቱሪስቶችና እንግዶች ምቹ ማረፊያ እንደሚሆንም ገልጸዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቅርቡ የተመረቀው የአርባ ምንጭ ኮንፈረንስ ሪዞርት የቱሪዝም መዳረሻዎችን ከማስፋፋት ባለፈ የሀገር የኢኮኖሚ አቅምን ከፍ ለማድረግ ሚናው የጎላ ነው።

ሪዞርቱ ከ1ሺህ 300 በላይ ሰዎችን የሚያስተናግድ የስብሰባ አዳራሽና በሐይቅ ላይ የተገነባ ልዩ ተንሳፋፊ ሬስቶራንትን ያካተተ እንደሆነም በወቅቱ ተመላክቷል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩም "ሪዞርቱ የኮንፈረንስ ቱሪዝምን በማስፋፋት ኢትዮጵያን የዓለም አቀፍ መድረኮች ማዕከል የማድረግ ራዕያችንን ያጠናክራል፤ ለአካባቢውም ማህበረሰብ ሰፊ የሥራ ዕድል ፈጥሯል" ሲሉ በወቅቱ መግለጻቸው የሚታወስ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026

የአየር ማረፊያው ለአገልግሎት መብቃት የአካባቢውን የንግድ፣ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ የሚያነቃቃ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 5 /2018 (ኢዜአ)፦የአየር ማረፊያው ለአገልግሎት መብቃትም የአካባቢውን የንግድ፣የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ በማ...

Jul 13, 2026

የኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ትብብርን ለማጠናከር ምቹ ምህዳር ፈጥሯል

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የተገበረችው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያና የዲጂታል አገልግሎት መስፋፋት የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ትብብርን ለማጠና...

Jul 9, 2026