የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ማእከሉ ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠትና ብልሹ አሰራርን ለማስቀረት እያገዘ ነው

Aug 13, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህር ዳር ፤ነሀሴ 6/2018 (ኢዜአ)፡ -የባህር ዳር መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ቀልጣፋ አገልግሎት ከመስጠት ባለፈ ብልሹ አሰራርን ለማስቀረት አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን የባህር ዳር ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ።

መንግስት መሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎትን በማስፋፋት ዜጎች ቀልጣፋና ዘመናዊ አገልግሎት እንዲያገኙ በማድረግ በዘርፉ የሚስተዋለውን የመልካም አስተዳደር ችግር እየፈታ ይገኛል።


እንዲሁም ዜጎች በአንድ ቦታ የተቀናጀ አገልግሎት እንዲያገኙ በማድረግ ከአላስፈላጊ ወጭና እንግልት ከመታደግ ባለፈ ብልሹ አሰራርን እያስቀረም ይገኛል።

ከዚሁ ጉዳይ ጋር በተገናኘ ኢዜአ ያነጋገራቸው የባህርዳር ከተማ ነዋሪዎች መሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎት ግልጽና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ የረዳቸው መሆኑን ተናግረዋል ።

ከነዋሪዎቹ መካከል አቶ አብርሃም ያረጋል እንደገለጹት፣ የባህር ዳር መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ከተማዋን የሚመጥን አግልግሎት እየሰጠ ነው።


መንጃ ፈቃድ ለማደስ ወደ ማእከሉ መምጣታቸውን ጠቁመው ቀደም ሲል ከሁለት ቀን በላይ ይወስድ የነበረው እድሳቱ በማእከሉ ከ30 ደቂቃ ባነሰ ጊዜ ውስጥ አገልግሎቱን ማግኘታቸውን ተናግረዋል ።

የሰራተኞቹም መልካም መስተንግዶ እንዲሁም ግልጽነትና ፍትሃዊነት የሰፈነበት አሰራር አስደሳች መሆኑን ጠቁመው በዚህ ረገድ ብልሹ አሰራር እንዲወገድ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ጠቁመዋል።

ሌላዋ የከተማው ነዋሪ ውባየሁ ጥጋቡ በበኩላቸው የወሳኝ ኩነት መረጃዎችን ለማስፈጸም ከዚህ ቀደም ሁለት ቦታ መሄድ ይጠይቅ እንደነበር አስታውሰው በማእከሉ በሚሰጠው የተቀናጀ አገልግሎት ችግሩ መፈታቱን ተናግረዋል ።

በማእከሉ ምንም አይነት መጉላላት ሳይገጥማቸው ፈጣንና ባጭር ጊዜ ውስጥ የተሳለጠ አገልግሎት ማግኘታቸውን አስረድተዋል።


የባህር ዳር መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት አስተባባሪ አቶ ማስረሻ ፈንታ በማእከሉ 14 ተቋማት አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን ተናግረዋል።

በተቋማቱ 91 የተለያዩ አገልግሎቶች እየተሰጡ መሆኑን አመልክተዋል።

በማእከሉ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመታገዝ በሚሰጠው አገልግሎት በየቀኑ እስከ 400 የሚደርሱ ደንበኞችን የማስተናገድ አቅም መፈጠሩን ተናግረዋል።

ማእከሉ ስራ ከጀመረበት ከመስከረም 2018 ዓ.ም ጀምሮ እስካሁን ከ75 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ተገልጋዮች አገልግሎት መስጠቱ ተመላክቷል ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026

የአየር ማረፊያው ለአገልግሎት መብቃት የአካባቢውን የንግድ፣ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ የሚያነቃቃ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 5 /2018 (ኢዜአ)፦የአየር ማረፊያው ለአገልግሎት መብቃትም የአካባቢውን የንግድ፣የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ በማ...

Jul 13, 2026

የኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ትብብርን ለማጠናከር ምቹ ምህዳር ፈጥሯል

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የተገበረችው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያና የዲጂታል አገልግሎት መስፋፋት የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ትብብርን ለማጠና...

Jul 9, 2026